La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




2 ሳሙኤል 10:15 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

ሶር​ያ​ው​ያ​ንም በእ​ስ​ራ​ኤል ፊት እንደ ተሸ​ነፉ ባዩ ጊዜ በአ​ን​ድ​ነት ተሰ​በ​ሰቡ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ሶርያውያን በእስራኤላውያን እንደ ተሸነፉ ባዩ ጊዜ፣ እንደ ገና ተሰባሰቡ።

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

ሶርያውያን በእስራኤላውያን እንደ ተሸነፉ ባዩ ጊዜ፥ እንደገና ተሰባሰቡ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ሶርያውያን በእስራኤላውያን ድል እንደ ተመቱ በተገነዘቡ ጊዜ ሠራዊታቸውን ሁሉ በአንድነት አሰባሰቡ፤

Ver Capítulo

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

ሶርያውያንም በእስራኤል ፊት እንደ ተሸነፉ ባዩ ጊዜ በአንድነት ተሰበሰቡ።

Ver Capítulo



2 ሳሙኤል 10:15
11 Referencias Cruzadas  

የአ​ሞን ልጆ​ችም ሶር​ያ​ው​ያን እንደ ሸሹ ባዩ ጊዜ እነ​ርሱ ደግሞ ከአ​ቢሳ ፊት ሸሹ፤ ወደ ከተ​ማ​ዪ​ቱም ገቡ፤ ኢዮ​አ​ብም ከአ​ሞን ልጆች ዘንድ ተመ​ልሶ ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ገባ።


አድ​ር​አ​ዛ​ርም ልኮ በካ​ላ​ማቅ ወንዝ ማዶ የነ​በ​ሩ​ትን ሶር​ያ​ው​ያን ሰበ​ሰ​ባ​ቸው፤ ወደ ኤላ​ምም መጡ፤ የአ​ድ​ር​አ​ዛ​ርም ሠራ​ዊት አለቃ ሶቤቅ በፊ​ታ​ቸው ነበረ።


ዳዊ​ትም ደግሞ እስከ ኤፍ​ራ​ጥስ ወንዝ ግዛት ለማ​ስ​ፋ​ፋት በሄደ ጊዜ የሱ​ባን ንጉሥ የረ​አ​ብን ልጅ አድ​ር​አ​ዛ​ርን መታ።


አሕ​ዛብ ለምን ዶለቱ? ወገ​ኖ​ችስ ለምን ከንቱ ይና​ገ​ራሉ?


የእ​ሳት ኀይ​ልን አጠፉ፤ ከሰ​ይፍ ስለት አመ​ለጡ፤ ከድ​ካ​ማ​ቸው በረቱ፤ በጦ​ር​ነት ኀይ​ለ​ኞች ሆኑ፤ የባ​ዕድ ጭፍ​ሮ​ች​ንም አባ​ረሩ።


እን​ዲ​ህም ሆነ፤ የአ​ሶር ንጉሥ ኢያ​ቢስ ይህን በሰማ ጊዜ ወደ ማሮን ንጉሥ ወደ ዮባብ፥ ወደ ስሚ​ዖን ንጉሥ፥ ወደ አዚ​ፍም ንጉሥ፥


እነ​ዚ​ህም ነገ​ሥ​ታት ሁሉ ተሰ​ብ​ስ​በው መጡ፤ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም በማ​ሮን ውኃ አጠ​ገብ አንድ ሆነው ተያ​ያ​ዙ​አ​ቸው።