ፍልስጥኤማውያንም ሳኦልንና ልጆቹን በእግር በእግራቸው ተከትለው አባረሩአቸው፤ ፍልስጥኤማውያንም የሳኦልን ልጆች ዮናታንንና አሚናዳብን ሜልኪሳንም ገደሉ።
1 ዜና መዋዕል 10:3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ሰልፍም በሳኦል ላይ ጠነከረ። ቀስተኞችም አግኝተው ወጉት፤ ከቀስቶችም ኀይል የተነሣ ተጨነቀ። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ውጊያው በሳኦል ላይ በረታበት፤ ቀስተኞችም ደርሰው ክፉኛ አቈሰሉት። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ውጊያውም በሳኦል ላይ ጠነከረ፥ ቀስተኞችም አገኙት፤ እነርሱም አቈሰሉት። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ሳኦል በነበረበት ግንባር ጦርነቱ እጅግ ተፋፍሞ ስለ ነበር ሳኦል በጠላት ፍላጻ ተመትቶ ክፉኛ ቈሰለ፤ መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ሰልፍም በሳኦል ላይ ጠነከረ፤ ቀስተኞችም አገኙት፤ ከቀስተኞቹም የተነሣ ተጨነቀ። |
ፍልስጥኤማውያንም ሳኦልንና ልጆቹን በእግር በእግራቸው ተከትለው አባረሩአቸው፤ ፍልስጥኤማውያንም የሳኦልን ልጆች ዮናታንንና አሚናዳብን ሜልኪሳንም ገደሉ።
ሳኦልም ጋሻ ጃግሬውን፥ “እነዚህ ቈላፋን መጥተው እንዳይዘብቱብኝ ሰይፍህን መዝዘህ ውጋኝ” አለው። ጋሻ ጃግሬው ግን እጅግ ፈርቶ ነበርና እንቢ አለ። ሳኦልም ሰይፉን ወስዶ በላዩ ወደቀ።