በጽዮን መለከትን ንፉ፤ በቅዱሱ ተራራዬም የማስጠንቀቂያውን ድምፅ አሰሙ። በምድሪቱ የሚኖሩ ሁሉ ይንቀጥቀጡ፤ የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና፤ እርሱም በደጅ ነው።
ዘኍል 10:7 - አዲሱ መደበኛ ትርጒም ማኅበሩን ለመሰብሰብ መለከቶች ይነፉ፤ ነገር ግን ድምፁ አይጩኽ። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ጉባኤውም በሚሰበሰብበት ጊዜ ንፉ፥ ነገር ግን የማስጠንቀቂያውን መለከት ከፍ ባለ ድምፅ አታሰሙ። አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ማኅበሩን በአንድነት እንዲሰበሰቡ ለማድረግ መለከት ትነፋለህ፤ ነገር ግን የማስጠንቀቂያውን ድምፅ አታሰማም፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ጉባኤውም በሚሰበሰብበት ጊዜ ያለ ምልክት ትነፉታላችሁ። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ጉባኤውም በሚሰበሰብበት ጊዜ ንፉ፥ ነገር ግን ድምፁን ከፍ አታድርጉት። |
በጽዮን መለከትን ንፉ፤ በቅዱሱ ተራራዬም የማስጠንቀቂያውን ድምፅ አሰሙ። በምድሪቱ የሚኖሩ ሁሉ ይንቀጥቀጡ፤ የእግዚአብሔር ቀን ቀርቧልና፤ እርሱም በደጅ ነው።