ዘካርያስ 5:10 - አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም እኔም ከእኔ ጋር ይነጋገር የነበረውን መልአክ “ቅርጫቱን ወዴት ነው የሚወስዱት?” ብዬ ጠየቅሁት። አዲሱ መደበኛ ትርጒም ከእኔ ጋራ ይነጋገር የነበረውንም መልአክ፣ “ቅርጫቱን የሚወስዱት ወዴት ነው?” አልሁት። መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ከእኔም ጋር ይነጋገር የነበረውን መልአክ፦ “እነዚህ የኢፍ መስፈሪያውን ወዴት ይወስዱታል?” አልኩት። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ከእኔም ጋር ይነጋገር የነበረውን መልአክ፦ እነዚህ የኢፍ መስፈሪያውን ወዴት ይወስዱታል? አልሁት። መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) ከእኔም ጋር ይነጋገር የነበረውን መልአክ፦ እነዚህ የኢፍ መስፈሪያውን ወዴት ይወስዱታል? አልሁት። |
ቀና ብዬ ስመለከት እነሆ ሁለት ሴቶች እየበረሩ ወደ እኔ መጡ፤ ክንፎቻቸውም እንደ ሽመላ ክንፎች ብርቱዎች ነበሩ። እነርሱም ያንን ቅርጫት ከመሬት አንሥተው ወደ ሰማይ ይዘውት በረሩ።