La Biblia Online

Anuncios


Toda la Biblia A.T. N.T.




መዝሙር 119:35 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

እርሷን ወድጃለሁና የትእዛዝህን መንገድ ምራኝ።

Ver Capítulo

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

በርሷ ደስ ይለኛልና፣ በትእዛዝህ መንገድ ምራኝ።

Ver Capítulo

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

ትእዛዞችህ ስለሚያስደስቱኝ እንድፈጽማቸው እርዳኝ።

Ver Capítulo



መዝሙር 119:35
19 Referencias Cruzadas  

ነገር ግን በጌታ ሕግ ደስ የሚለው፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት የሚያስብ።


በድንጋጌዎችህ ደስ ይለኛል፥ ቃልህንም አልረሳም።


ትእዛዛትህን መርጫለሁና እጅህ የሚያድነኝ ይሁን።


የድንጋጌዎችህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፥ ተኣምራትህንም አሰላስላለሁ።


ልቤን ወደ ምስክርህ አዘንብል፥ ወደ ስስትም አይሁን።


ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ።


አቤቱ፥ መንገድህን አመልክተኝ፥ ፈለግህንም አስተምረኝ።


መንገድዋ የደስታ መንገድ ነው፥ ጎዳናዋም ሁሉ ሰላም ነው።


የጥበብን መንገድ አስተማርሁህ፥ በቀናች ጎዳና መራሁህ።


የጻድቃን መንገድ ግን እንደ ንጋት ብርሃን ነው፥ ሙሉ ቀን እስኪሆንም ድረስ እየተጨመረ ይበራል።


እኔ በጽድቅ መንገድ እሄዳለሁ፥ በፍርድም ጎዳና መካከል፥


ብዙ ሕዝቦችም መጥተው እንዲህ ይላሉ፤ “ኑ፤ ወደ ጌታ ተራራ፤ ወደ ያዕቆብ አምላክ ቤት እንውጣ፤ እርሱ መንገዱን ያስተምረናል፤ በጎዳናውም እንሄዳለን።” ሕግ ከጽዮን፤ የእግዚአብሔር ቃል ከኢየሩሳሌም ይወጣልና።


ታዳጊህ፥ የእስራኤል ቅዱስ፥ ጌታ እንዲህ ይላል፦ እኔ የሚረባህን ነገር የማስተምርህ በምትሄድባትም መንገድ የምመራህ አምላክህ ጌታ ነኝ።


በውስጣዊ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛልና፥


በጎ ፈቃዱን እንድትፈልጉና እንድታደርጉ ሁለቱንም በእናንተ ውስጥ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና።


በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን በእናንተ እያደረገ፥ ፈቃዱን ትፈጽሙ ዘንድ በመልካም ሥራ ሁሉ ፍጹማን ያድርጋችሁ፤ ለእርሱ እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።


ትእዛዛቱን እንድንጠብቅ፥ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም።