ኢሳይያስ 28:24 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በውኑ ገበሬ ሊዘራ ሁልጊዜ ያርሳልን? ወይስ መሬቱን ሲገለብጥ፥ ዐፈሩን ሲያለሰልስ ይከርማል? አዲሱ መደበኛ ትርጒም ገበሬ ሊዘራ መሬቱን ሲያዘጋጅ ያለ ማቋረጥ ያርሳልን? ጓሉን ሲከሰክስ፣ ዐፈሩን ሲያለሰልስ ይከርማልን? አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም ማሳውን ለዘርና ለተክል ለማዘጋጀት ያለማቋረጥ ሲያርስና ጓሉን እያፈረሰ ሲጐለጒል የሚኖር ገበሬ አለን? የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) በውኑ ገበሬ ሊዘራ ሁልጊዜ ያርሳልን? ወይስ ምድሩን ከማረሱ አስቀድሞ ዘርን ይዘራልን? ጓሉንስ ይከሰክሳልን? መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት) በውኑ ገበሬ ሊዘራ ሁልጊዜ ያርሳልን? ወይስ ሁልጊዜ እርሻውን ይገለግላልን? |