ሰው ሆዱን ከአፉ ፍሬ ይሞላል፥ ከከንፈሩም ፍሬ ይጠግባል።
ሰው በአንደበቱ ፍሬ ሆዱ ይጠግባል፤ በከንፈሩም ምርት ይረካል።
የሰው ሆድ ከአፉ ፍሬ ይሞላል፥ ከንፈሩም ከሚያፈራው ይጠግባል።
ሰው በሚናገረው የንግግር ውጤት በመርካት ተደስቶ ይኖራል።
ደግ ሰው ከጽድቅ ፍሬ መልካምን ይበላል፤ የዐመፀኞች ነፍሳት ግን በጨርቋነታቸው ይጠፋሉ።
ልበ ትዕቢተኛ ከራሱ መንገድ ይጠግባል። ደግ ሰውም ከራሱ ዐሳብ ይጠግባል።
ወንድሙን የሚረዳ ወንድም እንደ ጸናችና ከፍ እንዳለች ከተማ ነው። በጽኑ መሠረትም እንደ ታነጸ ሕንጻ የጸና ነው።
እነርሱን በልብህ ብትጠብቅ፥ በከንፈሮችህ በአንድነት ደስ ያሰኙሃል።
በጎ ዕውቀትን ትሰማ ዘንድ፥ ለሚጠይቁህም የእውነት ቃልን ትመልስ ዘንድ ነዋሪ ቃልን አስተምርሃለሁ።