ደመናውን ልብሱ፣ ጨለማንም መጠቅለያው አደረግሁለት፣
ምድርም ቅርጽ የለሽና ባዶ ነበረች። የምድርን ጥልቅ ስፍራ ሁሉ ጨለማ ውጦት ነበር። የእግዚአብሔርም መንፈስ በውሆች ላይ ይረብብ ነበር።
ድንበር ወሰንሁለት፤ መዝጊያና መወርወሪያውን አበጀሁለት።
“ባሕር ከማሕፀን በወጣ ጊዜ፣ በር የዘጋበት ማን ነው?
ወደ ሰማይ የወጣ፣ የወረደስ ማነው? ነፋስን በእጁ ሰብስቦ የያዘ ማነው? ውሆችንስ በመጐናጸፊያው የጠቀለለ ማነው? የምድርን ዳርቻዎች ሁሉ የወሰነ ማነው? ስሙ ማን ነው? የልጁስ ስም ማን ይባላል? የምታውቅ ከሆነ እስኪ ንገረኝ!