የከተማዪቱ ከብት ማሰማሪያ ቦታ፣ በሰሜን ሁለት መቶ ዐምሳ ክንድ፣ በደቡብ ሁለት መቶ ዐምሳ ክንድ፣ በምሥራቅ ሁለት መቶ ዐምሳ ክንድ፣ በምዕራብም ሁለት መቶ ዐምሳ ክንድ ይሆናል።
የከተማዪቱም መጠን በሰሜን አራት ሺሕ ዐምስት መቶ ክንድ፣ በደቡብ አራት ሺሕ ዐምስት መቶ ክንድ፣ በምሥራቅ አራት ሺሕ ዐምስት መቶ ክንድ፣ የምዕራቡም እንዲሁ አራት ሺሕ ዐምስት መቶ ክንድ ይሆናል።
ከዚህ የሚቀረው፣ የተቀደሰውን ክፍል የሚያዋስነውና በተጓዳኝ ያለው ቦታ በምሥራቅ ዐሥር ሺሕ ክንድ፣ በምዕራብ ዐሥር ሺሕ ክንድ ይሆናል። ምርቱም ለከተማዪቱ ሠራተኞች ምግብ ይሆናል።