እንግዲህ ብልቶች ብዙ ናቸው፣ አካል ግን አንድ ነው።
እንዲሁም እኛ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ አንድ አካል ነን። እያንዳንዳችንም የሌላው ብልት ነን።
አካል ብዙ ብልቶች ቢኖሩትም አንድ አካል ነው፤ ነገር ግን ብልቶች ብዙ ቢሆኑም አካል አንድ ነው። ክርስቶስም እንደዚሁ ነው።
አካል የተሠራው ከብዙ ብልቶች እንጂ ከአንድ ብልት አይደለም።
ሁሉም አንድ ብልት ቢሆን ኖሮ አካል ከየት ይገኝ ነበር?
ዐይን እጅን፣ “አታስፈልገኝም” ሊለው አይችልም፤ ራስም እግርን፣ “አታስፈልገኝም” ሊለው አይችልም።