Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -

ይህ መፅሐፍ በእግዚአብሔር አልተነፀረም እና የክርስቲያን ካኖን ወይም የአይሁድ ታናክ ክፍል አይደለም። ለታሪክና ለጥናት ዓላማ ብቻ ይታያል። ሙሉ ማብራሪያን ይመልከቱ

መጽ​ሐፈ ተግ​ሣጽ 2 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ጠል በመ​ከር ዝና​ምም በበጋ ጥቅም እን​ደ​ሌ​ለው፥ እን​ዲሁ ለሰ​ነፍ ክብር አይ​ገ​ባ​ውም።

2 እን​ደ​ሚ​ተ​ላ​ለፍ ድን​ቢጥ፥ ወዲ​ያና ወዲ​ህም እን​ደ​ሚ​በ​ርር ጨረባ፥ እን​ዲሁ ከንቱ ርግ​ማን በማ​ንም ላይ አይ​ደ​ር​ስም።

3 አለ​ንጋ ለፈ​ረስ፥ መው​ጊያ ለአ​ህያ እንደ ሆነ፥ እን​ደ​ዚ​ሁም በትር ለሰ​ነፍ ጀርባ ነው።

4 ልጄ ሆይ፥ አንተ ደግሞ እር​ሱን እን​ዳ​ት​መ​ስል፥ ለሰ​ነፍ እንደ ስን​ፍ​ናው አት​መ​ል​ስ​ለት።

5 ነገር ግን ለራሱ ጠቢብ የሆነ እን​ዳ​ይ​መ​ስ​ለው፥ ለሰ​ነፍ እንደ ስን​ፍ​ናው መል​ስ​ለት።

6 በሰ​ነፍ መል​እ​ክ​ተኛ እጅ ነገ​ርን የሚ​ልክ፥ በእ​ግ​ሮቹ ውር​ደ​ትን ያመ​ጣል።

7 የአ​ን​ካሳ እግ​ሮች አካ​ሄድ ልዩ ነው፥ እን​ዲ​ሁም በደል በሰ​ነ​ፎች አፍ ነው።

8 ለሰ​ነፍ ክብ​ርን የሚ​ሰጥ ድን​ጋ​ይን በወ​ን​ጭፍ እን​ደ​ሚ​ያ​ስር ነው።

9 እሾህ በሰ​ካ​ራም እጅ እን​ደ​ሚ​ሰካ፥ እን​ዲ​ሁም መገ​ዛት በሰ​ነ​ፎች እጅ ነው።

10 የአ​ላ​ዋቂ ሰው​ነት ሁሉ ብዙ ይታ​ወ​ካል፥ ዐሳቡ ይበ​ታ​ተ​ና​ልና።

11 ወደ ትፋቱ የሚ​መ​ለስ ውሻ የተ​ጠላ እን​ደ​ሆነ በክ​ፋቱ ወደ ኀጢ​አቱ የሚ​መ​ለስ አላ​ዋ​ቂም እን​ዲሁ ነው። ኀጢ​አ​ትን የም​ታ​መጣ ኀፍ​ረት አለች፤ ክብ​ር​ንና ጸጋን የሚ​ያ​መጣ ኀፍ​ረ​ትም አለ።

12 ለራሱ ጠቢብ የሆነ የሚ​መ​ስ​ለ​ውን ሰው አየሁ፥ ከእ​ርሱ ይልቅ ለአ​ላ​ዋቂ እጅግ ተስፋ አለው።

13 ታካች ሰው በላ​ኩት ጊዜ፥ “አን​በሳ በመ​ን​ገድ አለ፤ በሜ​ዳም ገዳ​ዮች አሉ” ይላል።

14 ሣንቃ በማ​ጠ​ፊ​ያው ላይ እን​ደ​ሚ​ዞር፥ እን​ዲሁ ታካች ሰው በአ​ል​ጋው ላይ ይመ​ላ​ለ​ሳል።

15 ታካች ሰው እጁን በብ​ብቱ ይሸ​ሽ​ጋል፤ ወደ አፉም ይመ​ል​ሳት ዘንድ ለእ​ርሱ ድካም ነው።

16 ታካች ሰው መል​እ​ክ​ትን በአ​ጥ​ጋቢ ሁኔታ ከሚ​መ​ልስ ሰው ይልቅ፥ ለራሱ ጠቢብ የሆነ ይመ​ስ​ለ​ዋል።

17 አልፎ በሌ​ላው ጥል የሚ​ደ​ባ​ለቅ፥ የው​ሻን ጅራት እን​ደ​ሚ​ይዝ ነው።

18 ይድኑ ዘንድ የሚ​ወ​ድዱ ለሰው ነገ​ርን እን​ደ​ሚ​ያ​ወጡ እን​ደ​ዚሁ ነገ​ርን የሚ​ቀ​በል አስ​ቀ​ድሞ ይወ​ድ​ቃል፥

19 ባል​ን​ጀ​ራ​ቸ​ውን የሚ​ያ​ታ​ልሉ ሁሉ እን​ደ​ዚሁ ናቸው፤ ካወ​ቁ​ባ​ቸ​ውም በኋላ በጨ​ዋታ አደ​ረ​ግ​ነው ይላሉ።

20 በዕ​ን​ጨት መታ​ጣት እሳት ይጠ​ፋል፥ በዕ​ን​ጨት ብዛ​ትም እሳት ይነ​ድ​ዳል፥ ቍጡ በሌ​ለ​በ​ትም ዘንድ ጠብ ጸጥ ይላል።

21 ከሰል ፍምን፥ ዕን​ጨ​ትም እሳ​ትን እን​ዲ​ያ​በዛ፥ እን​ዲሁ ተሳ​ዳቢ ሰው ለጠ​ብና ለክ​ር​ክር ነው።

22 የአ​ታ​ላ​ዮች ቃል ደካማ ነው፥ ነገር ግን የም​ሕ​ረት መዝ​ገ​ቦ​ችን ይሰ​ብ​ራል።

23 በሐ​ሰት የሚ​ሰጥ ብር እንደ ገል ነው፥ በሸ​ክላ ዕቃ ላይ የሚ​ለ​በጥ ብር ግብዝ እንደ ሆነ እን​ደ​ዚ​ሁም ልዝ​ቦች ከን​ፈ​ሮች ያዘ​ነች ልብን ይሸ​ፍ​ናሉ።

24 ጠላት እያ​ለ​ቀሰ በከ​ን​ፈሩ ተስፋ ይሰ​ጣል፥ በልቡ ግን ተን​ኮ​ልን ያኖ​ራል።

25 ጠላ​ትህ በታ​ላቅ ድምፅ ደስ ቢያ​ሰ​ኝህ አት​መ​ነው፥ በልቡ ሰባት ክፋ​ቶች አሉ​በ​ትና።

26 ጠላ​ት​ነ​ቱን የሚ​ሸ​ሽግ ተን​ኰ​ልን ይሰ​በ​ስ​ባል፥ ዐዋቂ ግን በጉ​ባኤ መካ​ከል በደ​ሉን ይገ​ል​ጣል።

27 ጕድ​ጓ​ድን ለባ​ል​ን​ጀ​ራው የሚ​ምስ ራሱ ይወ​ድ​ቅ​በ​ታል፥ ድን​ጋ​ይ​ንም የሚ​ያ​ን​ከ​ባ​ልል በላዩ ይገ​ለ​በ​ጥ​በ​ታል።

28 ሐሰ​ተኛ ምላስ እው​ነ​ትን ትጠ​ላ​ለች፥ ዝም የማ​ይል አፍም ክር​ክ​ርን ያመ​ጣል።

ተከተሉን:



ማስታወቂያዎች