መጽሐፈ ጥበብ 18:21 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) አንድ ንጽሕ ሰው ከመዓቱ አድኗቸዋልና። የተቀደሱ መሣሪያዎቹን፥ ጸሎቱንና የስርየት ዕጣን በመያዝ ቁጣውን ተጋፈጠው፤ አገልጋይህ መሆኑንም በማስመስከር መዓቱን አስወገደ። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ነውር የሌለበት ሰው ጸሎት የሚጸልይበትን፥ ዕጣንም የሚያጥንበትን የአገልግሎት መሣሪያ፥ ልብሰ መትከፉን ይዞ ፈጥኖ ተዋግቶአልና ኀጢአታቸውን ለማቃለል ባለሟልነትን አገኘ፤ መዓቱን ተቃወመ፥ መቅሠፍቱንም ጸጥ አደረገ። በዚህም ያንተ መልእክተኛ እንደ ሆነ ራሱን አስታወቀ። |