መጽሐፈ ጦቢት 5:14 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ጦቢትም “ወንድሜ ሆይ እንኳን በደኀና መጣህ፥ ስለ ቤተሰብህ እርግጡን ለማወቅ በመሻቴ አትቀየመኝ፥ ወንድማችን መሆንህ ከጥሩ ዘር መወለድህ አወቅሁ፤ የታላቁ የሸማይያ ሁለት ልጆች አናንያንና ናታንን አውቃቸዋለሁ፤ ከኔ ጋር ኢየሩሳሌም ይሄዱ ነበር አብረን እንሰግድ ነበር። ከእምነታቸው ንቅንቅ አላሉም፤ ዘመዶችህ ደጐች ናቸው፥ ከመልካም ዘር ተወልደሃል፤ እንኳን ደኀና መጣህ” አለው። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ወንድሜ አንተ ግን ከደግ ቤተ ሰብ ነህ፤ ነገር ግን ንገረኝ፤ ደመወዝህን ምን እንስጥህ? በየቀኑ አንድ ድራህማ እንስጥህን? ምግብህስ ከልጄ ጋር ይሁን? |