መጽሐፈ ጦቢት 13:16 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) ምክንያቱም ኢየሩሳሌም ለዘለዓለም ቤቱ ሆና እንደ አዲስ ትታነጻለችና፥ የአንቺን ክብር ለማየትና፥ የሰማዩን ንጉሥ ለማመሰገን፥ ከቤተሰቦቼ አንዱ እንኳ ቢቀር፥ ምንኛ ደስታ ነበር፤ የኢየሩሳሌም በሮች ከሰንፔርና ከኤመራልድ ይሠራሉ፥ ግንቦችሽም ከውድ ዐለቶች ይፈለፈላሉ፥ የኢየሩሳሌም ህንፃዎች ከወርቅ፥ ቅጥሮቻቸውም ከንጹህ ወርቅ ይሠራሉ፤ የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ኢየሩሳሌም ሰንፔር በሚባል ዕንቍ ትሠራለችና፥ ግድግዳዋ በመረግድና በከበረ ዕንቍ፥ አዳራሽዋና በሮችዋ በጠራ ወርቅ ይሠራሉና። |