መጽሐፈ ጦቢት 1:18 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ) በሰናክሬም የተገደሉትን ሁሉ ጭምር እቀብር ነበር። ሰናክሬም በተሳደበው ስድብ ምክንያት የሰማይ ንጉሥ ቀጥቶት ከይሁዳ ሸሽቶ በመጣ ጊዜ ተበሳጭቶ ነበርና ብዙ እስራኤላውያንን ገደለ፤ እሱ የገደላቸውን ሰዎች ሬሳ እየሰረቅሁ እቀብር ነበር፤ ሬሳቸውንም ሲፈልገው አያገኘውም ነበር። የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ) ንጉሥ ሰናክሬም ከይሁዳ ሸሽቶ በተመለሰ ጊዜ የገደላቸውን ሰዎች እኔ በስውር እቀብራቸው ነበር። እርሱ ተቈጥቶ ብዙዎችን ገድሎ ነበርና። ንጉሡም ሬሳቸውን አስፈለገ፥ አላገኘምም። |