በጣም ተቆጥቶ ያበረሩትን ሰዎች በቀለ በአይሁዳውያን ላይ ለመውጣት አሰበ፤ ስለዚህ ሠረገላ ነጂውን ሰረገለውን በፍጥነት እየነዳ እንዲሄድ አዘዘው፤ ግን በእርሱ ላይ ከሰማዩ ፍርድ ወድቆበት ነበር፤ በትዕቢት ተነፍቶ፥ “በደረስሁ ጊዜ ኢየሩሳሌምን የአይሁዳውያን መቃብር አደርጋታለሁ” ሲል ተናገረ።