የጉዳዮቹ ፈጻሚ አድርጐ የተወው ፊሊጶስ በአንጾኪያ እንደተነሣበት በሰማ ጊዜ አንጥዮኩስ ተደናገጠ። ከአይሁዳውያን ጋር የሰላም ድርድር ማድረግና መስማማት ፈለገ፤ ትክክለኛ የሆነውን ነገር ሁሉ ለማድረግ ማለ፤ ከእነርሱ ጋር ታረቀ። መሥዋዕት በማቅረብ ቤተ መቅደስን አከበረ፤ ለተቀደሰው ቦታ መልካም በማድረግ ልግስናውን ገለጸ።