Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -


Este libro no es inspirado por Dios y no forma parte del canon cristiano ni del Tanaj judío. Se muestra solo con fines históricos y de estudio. Ver explicación completa

መጽ​ሐፈ ተግ​ሣጽ 4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 ኃጥእ ማንም ሳያ​ሳ​ድ​ደው ይሸ​ሻል፤ ጻድቅ ግን እንደ አን​በሳ ተማ​ምኖ ይኖ​ራል።

2 በክ​ፉ​ዎች በደል መቅ​ሠ​ፍት ይነ​ሣል፤ ዐዋቂ ሰው ግን ፈጽሞ ያጠ​ፋ​ዋል።

3 በኀ​ጢ​አት የጸና ሰው ድሆ​ችን ይቀ​ማል፤ እን​ደ​ማ​ይ​ጠ​ቅም እንደ ከባድ ዝና​ብም ነው፥

4 ሕግን የሚ​ተ​ዉና ኀጢ​አ​ትን የሚ​ያ​ወ​ድሱ እን​ደ​ዚሁ ናቸው። ሕግ ጠባ​ቂ​ዎች ግን ለራ​ሳ​ቸው ቅጥ​ርን ይሠ​ራሉ።

5 ክፉ​ዎች ሰዎች ፍር​ድን አያ​ስ​ተ​ው​ሉም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚሹ ግን ሁሉን ያስ​ተ​ው​ላሉ።

6 ከሐ​ሰ​ተኛ ባለ​ጠጋ፥ በእ​ው​ነት የሚ​ሄድ ድሃ ይሻ​ላል።

7 ሕግን የሚ​ጠ​ብቅ ልጅ ዐዋቂ ነው፤ አመ​ን​ዝራ ሴትን የሚ​መ​ለ​ከት ግን ለጥ​ፋት ይዳ​ረ​ጋል፥ አባ​ቱ​ንም ያሰ​ድ​ባል።

8 በአ​ራ​ጣና በቅ​ሚያ ሀብ​ቱን የሚ​ያ​በዛ ለድሃ ለሚ​ራራ ያከ​ማ​ች​ለ​ታል።

9 ሕግን ከመ​ስ​ማት ጆሮ​ውን የሚ​መ​ልስ ሰው ጸሎቱ የተ​ናቀ ነው።

10 ቅኖ​ችን በክፉ መን​ገድ የሚ​ያ​ስት፥ እርሱ ወደ ጥፋት ይወ​ድ​ቃል፤ ዐመ​ፀ​ኞች ግን በመ​ል​ካም በኩል ያል​ፋሉ፥ ወደ ውስ​ጧም አይ​ገ​ቡም።

11 ባለ​ጠጋ ሰው ለራሱ ጠቢብ የሆነ ይመ​ስ​ለ​ዋል፤ አስ​ተ​ዋይ ድሃ ግን ይመ​ረ​ም​ረ​ዋል።

12 በጻ​ድ​ቃን ረድ​ኤት ብዙ ክብር አለ፤ በኃ​ጥ​ኣን መን​ገድ ግን ሰዎች ይጠ​ፋሉ።

13 በደ​ሉን የሚ​ሰ​ውር ሰው መን​ገዱ አይ​ቃ​ናም፤ የሚ​ና​ዘ​ዝና ራሱን የሚ​ዘ​ልፍ ግን ይወ​ደ​ዳል።

14 ስለ ጽድቅ ሁል​ጊዜ የሚ​ደ​ነ​ግጥ ሰው ብፁዕ ነው፤ ልቡን የሚ​ያ​ጸና ግን በክፉ ይወ​ድ​ቃል።

15 ራሱ ድሃ ሆኖ ሳለ ድሃ ሕዝ​ብን የሚ​ያ​ስ​ጨ​ንቅ ክፉ መኰ​ንን፥ እንደ ተራበ አን​በ​ሳና እንደ ተጠማ ተኵላ ነው።

16 አእ​ምሮ የጐ​ደ​ለው ንጉሥ ብዙ ግብ​ርን አስ​ገ​ባሪ ይሆ​ናል፤ ግፍን የሚ​ጠላ ግን ብዙ ዘመን ይኖ​ራል።

17 በሰው ደም የሚ​ገባ ዐመ​ፀኛ ሰው ወደ ጕድ​ጓድ በሚ​ገ​ባ​በት ጊዜ የሚ​ይ​ዘው የለም፥ ለነ​ፍሰ ገዳ​ይም ዋስ የሚ​ሆን ሰው ይሰ​ደ​ዳል፥ በደ​ኅ​ናም አይ​ኖ​ርም። ልጅ​ህን አስ​ተ​ም​ረው ይወ​ድ​ድ​ሃ​ልም፥ ለነ​ፍ​ስ​ህም ክብ​ርን ይሰ​ጣል። ዐመ​ፀኛ ሕዝብ ሕግን አይ​ሰ​ማም።

18 በጽ​ድቅ መን​ገድ የሚ​ሄድ ሰው ይረ​ዳል፥ በጠ​ማማ መን​ገድ የሚ​ሄድ ግን በወ​ጥ​መድ ይያ​ዛል።

19 ምድ​ሩን የሚ​ያ​ርስ እን​ጀ​ራን ይጠ​ግ​ባል፤ ሥራ ፈት​ነ​ትን የሚ​ያ​በዛ ግን ድህ​ነ​ትን ያበ​ዛል።

20 የታ​መነ ሰው እጅግ ይባ​ረ​ካል፤ ክፉ ሰው ግን ከቅ​ጣት አይ​ድ​ንም።

21 የጻ​ድ​ቃ​ንን ፊት የማ​ያ​ፍር ሰው ደግ አይ​ደ​ለም፥ እን​ዲህ ያለ ሰው በቍ​ራሽ እን​ጀራ ሰውን አሳ​ልፎ ይሰ​ጣል።

22 ምቀኛ ሰው ባለ​ጠጋ ለመ​ሆን ይቸ​ኩ​ላል፥ የሚ​ራራ ሰውም እን​ደ​ሚ​ገ​ዛው አያ​ው​ቅም።

23 በም​ላሱ ከሚ​ሸ​ነ​ግል ሰው ይልቅ የሰ​ውን መን​ገድ የሚ​ነ​ቅፍ እጅግ ክብ​ርን ያገ​ኛል።

24 ከአ​ባ​ቱና ከእ​ናቱ የሚ​ሰ​ርቅ፥ ኀጢ​አ​ት​ንም አል​ሠ​ራ​ሁም የሚል፥ የአ​ጥፊ ባል​ን​ጀራ ነው።

25 የሚ​ሳሳ ሰው ከን​ቱን ይፈ​ር​ዳል፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ታ​መን ግን በጥ​ን​ቃቄ ይኖ​ራል።

26 በልቡ ደስታ የሚ​ታ​መን ሰው እን​ደ​ዚሁ ሰነፍ ነው፤ በጥ​በብ የሚ​ሄድ ግን ይድ​ናል።

27 ለድሃ የሚ​ሰጥ አይ​ቸ​ገ​ርም፤ ዐይ​ኖ​ቹን የሚ​ያ​ዞር ግን በከ​ባድ ችግር ይኖ​ራል።

28 በኃ​ጥ​ኣን ቦታ ጻድ​ቃን ያለ​ቅ​ሳሉ፥ በእ​ነ​ርሱ ጥፋት ግን ጻድ​ቃን ይበ​ዛሉ።

Síguenos en:



Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos