1 ዜና መዋዕል 3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)1 በኬብሮን ለዳዊት የተወለዱለት ልጆች እነዚህ ናቸው። በኵሩ አምኖን ከኢይዝራኤላዊቱ ከአኪናሆም፥ ሁለተኛውም ዶለህያ ከቀርሜሎሳዊቱ ከአቢግያ፥ 2 ሦስተኛው አቤሴሎም ከጌድሶር ንጉሥ ከተልማይ ልጅ ከመዓካ፥ አራተኛው አዶንያስ ከአጊት፥ 3 አምስተኛው ሰፋጥያስ ከአቢጣል፥ ስድስተኛው ይትርኃም ከሚስቱ ከዔግላ። 4 እነዚህ ስድስቱ በኬብሮን ተወለዱለት፤ በዚያም ሰባት ዓመት ከስድስት ወር ነገሠ፤ በኢየሩሳሌምም ሠላሳ ሦስት ዓመት ነገሠ። 5 እነዚህ ደግሞ በኢየሩሳሌም ተወለዱለት፤ ከዓሚል ልጅ ከቤርሳቤህ ስማዕ፥ ሶባብ፥ ናታን፥ ሰሎሞን፥ አራት፤ 6 ኢያቤሔር፥ ኤልሳማ፥ ኤሊፋላት፥ 7 ናጌል፥ ናፌቅ፥ ያፍያ፥ 8 ኤልሳማ፥ ኤሊዳ፥ ኤልፋሌጥ፥ ዘጠኝ። 9 እነዚህ ሁሉ ከቁባቶቹ ልጆች በቀር የዳዊት ልጆች ነበሩ፤ ትዕማርም እኅታቸው ነበረች። 10 የሰሎሞንም ልጅ ሮብዓም ነበረ፤ ልጁ አቢያ፥ ልጁ አሳ፥ ልጁ ኢዮሣፍጥ፥ 11 ልጁ ኢዮራም፥ ልጁ አካዝያስ፥ ልጁ ኢዮአስ፥ 12 ልጁ አሜስያስ፥ ልጁ ዓዛርያስ፥ ልጁ ኢዮአታም፥ 13 ልጁ አካዝ፥ ልጁ ሕዝቅያስ፥ ልጁ ምናሴ፥ 14 ልጁ አሞጽ፥ ልጁ ኢዮስያስ። 15 የኢዮስያስም ልጆች፤ በኵሩ ዮሐናን፥ ሁለተኛውም ኢዮአቄም፥ ሦስተኛውም ሴዴቅያስ፥ አራተኛውም ሰሎም። 16 የኢዮአቄምም ልጆች፤ ልጁ ኢኮንያን፥ ልጁ ሴዴቅያስ። 17 የኢኮንያንም ልጆች አሤር፥ ሰላትያል፥ 18 መልኪራም፥ ፈዳያ፥ ሳንሳሮ፥ ይቃምያ፥ ሆሻማ፥ ነዳብያ ነበሩ። 19 የፈዳያም ልጆች ዘሩባቤልና ሰሜኤ ነበሩ፤ የዘሩባቤልም ልጆች፤ ሜሱላም፥ ሐናንያ፥ እኅታቸውም ሰሎሚት። 20 አሱባ፥ አሄል፥ በራክያ፥ ሐሳድያ፥ አስቦሴድ አምስት ናቸው። 21 የሐናንያም ልጆች ፈላጥያና ልጁ ኢያሴያ ነበሩ። ረፋያ ልጁ፥ አርና ልጁ፥ አብድዩ ልጁ፥ ሴኬንያ ልጁ። 22 የሴኬንያም ልጅ ሰማዕያ ነበረ። የሰማዕያም ልጆች ሐጡስ፥ ኢዮሔል፥ ቤርያሕ፥ ነዋድያ፥ ሳፌጥ ስድስት ነበሩ። 23 የነዋድያ ልጆች ኤልዮዔንኢ፥ ሕዝቅያስ፥ ዓዝሪቃም ሦስት ነበሩ። 24 የኤልዮዔናኢም ልጆች አዳይያ፥ ኤልያሴብ፥ ፈላያ፥ ዓቁብ፥ ዮሐናን፥ ዶላያ፥ ዓናኒ ሰባት ነበሩ። |