Biblia Todo Logo
La Biblia Online
- Anuncios -




መሳፍንት 9:48 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

48 አቤ​ሜ​ሌ​ክና ከእ​ርሱ ጋር ያሉ​ትም ሕዝብ ሁሉ ወደ ሄር​ሞን ተራራ ወጡ፤ አቤ​ሜ​ሌ​ክም በእጁ መጥ​ረ​ቢያ ወስዶ የዛ​ፉን ቅር​ን​ጫፍ ቈረጠ፤ አን​ሥ​ቶም በጫ​ን​ቃው ላይ ተሸ​ከ​መው፤ ከእ​ር​ሱም ጋር ለነ​በ​ሩት ሕዝብ፥ “እኔ ሳደ​ርግ ያያ​ች​ሁ​ትን፥ እና​ን​ተም ፈጥ​ና​ችሁ እኔ እን​ዳ​ደ​ረ​ግሁ አድ​ርጉ” አላ​ቸው።

Ver Capítulo Copiar

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

48 እርሱና ሰዎቹ ሁሉ ወደ ሰልሞን ተራራ ወጡ፤ አቢሜሌክም መጥረቢያ ወስዶ ጥቂት የዛፍ ቅርንጫፍ ቈረጠ፤ በትከሻውም ላይ አደረገ። የተከተሉትንም ሰዎች፣ “ፍጠኑ፤ እኔ ሳደርግ ያያችሁትን አድርጉ” ሲል አዘዛቸው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

48 እርሱና ሰዎቹ ሁሉ ወደ ሰልሞን ተራራ ወጡ፤ አቤሜሌክም መጥረቢያ ወስዶ ጥቂት የዛፍ ቅርንጫፍ ቈረጠ፤ በትከሻውምላይ አደረገ። የተከተሉትንም ሰዎች፥ “ፍጠኑ፤ እኔ ሳደርግ ያያችሁትን አድርጉ” ሲል አዘዛቸው።

Ver Capítulo Copiar

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

48 ስለዚህም ከተከታዮቹ ጋር ወደ ጻልሞን ተራራ ወጣ፤ ከዚያም መጥረቢያ ወስዶ ከዛፍ ላይ እንጨት በመቊረጥ በትከሻው ተሸከመ፤ ተከታዮቹም በፍጥነት እርሱ እንዳደረገው ያደርጉ ዘንድ ነገራቸው።

Ver Capítulo Copiar

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

48 አቤሜሌክና ከእርሱ ጋር ያሉትም ሕዝብ ሁሉ ወደ ሰልሞን ተራራ ወጡ፥ አቤሜሌክም በእጁ መጥረቢያ ወስዶ የዛፉን ቅርንጫፍ ቈረጠ፥ አንሥቶም በጫንቃው ላይ አደረገው፥ ከእርሱም ጋር ለነበሩት ሕዝብ፦ እኔ ሳደርግ ያያችሁትን፥ እናንተም ፈጥናችሁ እኔ እንዳደረግሁ አድርጉ አላቸው።

Ver Capítulo Copiar




መሳፍንት 9:48
7 Referencias Cruzadas  

እን​ዳ​ይ​ው​ጠኝ ከረ​ግ​ረግ አው​ጣኝ፤ ከጠ​ላ​ቶ​ችና ከጥ​ልቅ ውኃ አስ​ጥ​ለኝ።


የውኃ ማዕ​በል አያ​ስ​ጥ​መኝ፥ ጥል​ቁም አይ​ዋ​ጠኝ፥ ጕድ​ጓ​ዶ​ችም አፋ​ቸ​ውን በኔ ላይ አይ​ክ​ፈቱ፤


ለአ​ቤ​ሜ​ሌ​ክም በሰ​ቂማ ግንብ ውስጥ ያሉ ሰዎች ሁሉ አንድ ሆነው እንደ ተሰ​በ​ሰቡ ነገ​ሩት።


ሕዝ​ቡም ሁሉ እን​ዲሁ እያ​ን​ዳ​ን​ዳ​ቸው የዛ​ፉን ቅር​ን​ጫ​ፎች ቈረጡ፤ አቤ​ሜ​ሌ​ክ​ንም ተከ​ት​ለው በም​ሽጉ ዙሪያ አኖ​ሩ​አ​ቸው፤ ምሽ​ጉ​ንም በላ​ያ​ቸው በእ​ሳት አቃ​ጠ​ሉት፤ የሰ​ቂ​ማም ግንብ ሰዎች ሁሉ ደግሞ አንድ ሺህ የሚ​ያ​ህሉ ወን​ድና ሴት ሞቱ።


አቤ​ሜ​ሌ​ክም ወደ ግንቡ ሄደ። እነ​ር​ሱም ተዋ​ጉት። አቤ​ሜ​ሌ​ክም በእ​ሳት ሊያ​ቃ​ጥ​ለው ወደ ግንቡ ደጅ ቀረበ።


Síguenos en:

Anuncios


Anuncios


¡Síguenos en WhatsApp! Síguenos