አንተ አታላይ አንደበት ሆይ፤ ጐጂ ቃላትን ሁሉ ወደድህ!
ሐሰተኛ አንደበት ሆይ፤ ምን ይከፈልህ? ከዚህስ የባሰ ምን ይደረግብህ?
እግዚአብሔር ሆይ፤ ከክፉዎች እጅ ጠብቀኝ፤ እግሮቼንም ለመጥለፍ ከሚያደቡ ዐመፀኞች ሰውረኝ።
አፍህን ለክፋት አዋልህ፤ አንደበትህም ሽንገላን ጐነጐነ።