ተነሥና እርዳን! ስለ ምሕረትህ ስትል ተቤዠን።
ነፍሴ ከዐፈር ተጣበቀች፤ እንደ ቃልህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ።
አምላክ ሆይ፤ እስራኤልን ከመከራው ሁሉ አድነው።
እኔ ግን በተአማኒ ሕይወት እጓዛለሁ፤ አድነኝ፤ ምሕረትንም አድርግልኝ።
ትልቁንና ትንሹን ጋሻ ያዝ፤ እኔንም ለመርዳት ተነሥ።