እርሱም አሳያቸው፤ እነርሱም ከሰውየውና ከቤተ ሰቡ በቀር የከተማዪቱን ሕዝብ በሰይፍ ስለት ፈጁ።
ሰውየውም ወደ ኬጢያውያን ምድር ሄዶ ከተማ ሠራ፤ ስሟንም ሎዛ ብሎ ጠራት፤ እስከ ዛሬም የምትጠራው በዚሁ ስም ነው።