ኤሊሁ በመቀጠል እንዲህ አለ፤
ስለዚህ የቡዛዊው የባርክኤል ልጅ ኤሊሁ እንዲህ አለ፤ “እኔ በዕድሜ ታናሽ ነኝ፤ እናንተ ግን አዛውንቶች ናችሁ፤ ከዚህም የተነሣ የማውቀውን ለመናገር አልደፈርሁም፤ ፈርቼ ዝም አልሁ።
ስለዚህ ኢዮብ አፉን በከንቱ ይከፍታል፤ ዕውቀት አልባ ቃላትም ያበዛል።”
“በእግዚአብሔር ፈንታ ሆኜ የምለው አለኝ፤ ጥቂት ታገሠኝና እነግርሃለሁ።