“ኢዮብ እንዲህ ይላል፤ ‘እኔ ንጹሕ ነኝ፤ እግዚአብሔር ግን ፍትሕ ነሣኝ፤
እኔ በደለኛ እንዳልሆንሁ፣ ከእጅህም ሊያስጥለኝ ማንም እንደማይችል አንተ ታውቃለህ።
አምላክንም፣ ‘ትምህርቴ የጠራ፣ በዐይንህም ፊት የጸዳሁ ነኝ’ ትለዋለህ።
እንግዲህ ጕዳዬን ይዤ ቀርቤአለሁ፤ እንደሚፈርድልኝም ዐውቃለሁ።
ነገር ግን በእጄ ዐመፅ አይገኝም፤ ጸሎቴም ንጹሕ ነው።
“ ‘ተበደልሁ’ ብዬ ብጮኽ ማንም አይመልስልኝም፤ ድምፄን ከፍ አድርጌ ባሰማም፣ ፍትሕ አላገኝም።
“ፍትሕ የነሣኝ ሕያው እግዚአብሔርን! ነፍሴንም መራራ ያደረጋት፣ ሁሉን ቻይ አምላክን!
ጽድቅን እንደ ልብስ ለበስሁ፤ ፍትሕም መጐናጸፊያዬና ጥምጥሜ ነበር።
ኢዮብ በበኩሉ ራሱን እንደ ጻድቅ ቈጥሮ ስለ ነበር፣ እነዚህ ሦስት ሰዎች ለርሱ መልስ መስጠታቸውን ተዉ።
‘ኀጢአት የሌለብኝ ንጹሕ ነኝ፤ ከበደል ነጻ ነኝ፤ እድፈትም የለብኝም፤
የሚበጀንን እንምረጥ፣ መልካሙንም ዐብረን እንወቅ።
መለስ በሉ፤ ፍርደ ገምድል አትሁኑ፤ ጽድቄ ጸንታ ቆማለችና መለስ ብላችሁ አስተውሉ።
እግዚአብሔር ፍትሕን ያጣምማልን? ሁሉን ቻይ አምላክስ ጽድቅን ያጣምማልን?
በዐውሎ ነፋስ ይሰብረኛል፤ ቍስሌንም ያለ ምክንያት ያበዛል፤
ያዕቆብ ሆይ፤ ለምን እንዲህ ትላለህ? እስራኤል ሆይ፤ ለምን እንዲህ ትናገራለህ? “መንገዴ ከእግዚአብሔር ተሰውራለች፤ ፍርዴም በአምላኬ ቸል ተብላለች” ለምን ትላለህ?