Biblia Todo Logo
ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች
- ማስታወቂያዎች -



ኢዮብ 13:5

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

ምነው ዝም ብትሉ! ያ ከጥበብ ይቈጠርላችሁ ነበር።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

14 ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች  

በውኑ የአንተ መዘላበድ ሰውን ዝም ያሰኛልን? ስታፌዝስ የሚገሥጽህ የለም?

“ዝም በሉ፤ እኔ ልናገር፤ የመጣው ይምጣብኝ።

እንግዲህ ክርክሬን ስሙ፤ የከንፈሬንም አቤቱታ ስሙ።

ይህ ከንቱ ንግግር አያልቅምን? ትለፈልፍ ዘንድ የሚገፋፋህ ምንድን ነው?

“ይህን ንግግር የምትጨርሰው መቼ ነው? እስኪ ልብ ግዛ፤ ከዚያ በኋላ እንነጋገራለን።

“ነፍሴን የምታስጨንቋት፣ በቃልስ የምትደቍሱኝ እስከ መቼ ነው?

ተመልከቱኝና ተገረሙ፤ አፋችሁን በእጃችሁ ለጕሙ።

ኢዮብ በበኩሉ ራሱን እንደ ጻድቅ ቈጥሮ ስለ ነበር፣ እነዚህ ሦስት ሰዎች ለርሱ መልስ መስጠታቸውን ተዉ።

እንግዲህ እነርሱ መልስ ስላጡ፣ ጸጥ ብለውም ስለ ቆሙ፣ በትዕግሥት ልጠብቅን?

ቂል እንኳ ዝም ቢል ጠቢብ፣ አንደበቱንም ቢገዛ አስተዋይ ይመስላል።

በሥራ ብዛት ሕልም እንደሚታይ፣ ብዙ ቃል ባለበትም የሞኝ ንግግር ይገለጣል።

ስለዚህ አስተዋይ ሰው በእንዲህ ያለ ጊዜ ዝም ይላል፤ ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና።

የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፤ ይህን አስተውሉ፤ ሰው ሁሉ ለመስማት የፈጠነ፣ ለመናገር የዘገየ፣ ለቍጣም የዘገየ ይሁን፤




ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች