ርምጃዬን አሰፋህ፤ እግሮቼም አልተሰነካከሉም።
ወደ ሰፊ ስፍራ አወጣኝ፤ ደስ ተሰኝቶብኛልና አዳነኝ።
እግርህ እንዲሸራተት አይፈቅድም፤ የሚጠብቅህም አይተኛም።
አረማመዴ በመንገድህ ጸንቷል እግሮቼም አልተንሸራተቱም።
ከሥሬ ያለውን ስፍራ ለአረማመዴ አሰፋህልኝ፤ እግሬም አልተንሸራተተም።
የጽድቄ አምላክ ሆይ፤ በጠራሁህ ጊዜ መልስልኝ፤ ከጭንቀቴ አሳርፈኝ፤ ማረኝ፤ ጸሎቴንም ስማ።
እኔ፣ “እግሬ አዳለጠኝ” ባልሁ ጊዜ፣ እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ደግፎ ያዘኝ።
ስትሄድ ርምጃህ አይሰናከልም፤ ስትሮጥም አትደናቀፍም።
እርሱ የታማኝ አገልጋዮቹን እግር ይጠብቃል፤ ክፉዎች ግን በጨለማ ውስጥ ይጣላሉ። “ሰው በኀይሉ ድል አያደርግም፤