Biblia Todo Logo
የመስመር ላይ መጽሐፍ ቅዱስ
- ማስታወቂያዎች -




ኤርምያስ 14:18 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

18 ወደ ሜዳ ብወጣ፥ እነሆ በሰ​ይፍ የሞቱ አሉ፤ ወደ ከተ​ማም ብገባ፥ እነሆ በራብ የከሱ አሉ፤ ነቢ​ዩና ካህኑ ወደ​ማ​ያ​ው​ቋት ሀገር ሄደ​ዋ​ልና።”

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

18 ወደ ገጠር ብወጣ፣ በሰይፍ የተገደሉትን አያለሁ፤ ወደ ከተማ ብገባ፣ በራብ የወደቁትን አያለሁ ነቢዩም ካህኑም፣ ወደማያውቁት አገር ሸሽተዋል።’ ”

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

18 ወደ ሜዳ ብወጣ፥ እነሆ፥ በሰይፍ የሞቱ አሉ፤ ወደ ከተማም ብገባ፥ እነሆ፥ በራብ ደዌ የከሱ አሉ፤ ነቢዩና ካህኑም ወደማያውቁት አገር ሄደዋልና።’”

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

18 ወደየመስኩ ብወጣ በጦርነት የተገደሉ ሰዎችን ሬሳ አያለሁ፤ ወደ ከተማም ብገባ በራብ ለመሞት የሚያጣጥሩ ሰዎችን አያለሁ፤ ነቢያትና ካህናት የራሳቸውን ጉዳይ ይከታተላሉ፤ ነገር ግን የሚያደርጉትን አያውቁም።”

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

18 ወደ ሜዳ ብወጣ፥ እነሆ፥ በሰይፍ የሞቱ አሉ፥ ወደ ከተማም ብገባ፥ እነሆ፥ በራብ የከሱ አሉ፥ ነቢዩና ካህኑም ወደማያውቋት አገር ሄደዋልና።

ምዕራፉን ተመልከት ቅዳ




ኤርምያስ 14:18
19 ተሻማሚ ማመሳሰሪያዎች  

ጩኸ​ትና ፍጅ​ትም የተ​ሞ​ላ​ብሽ ከተማ ሆይ፥ ቍስ​ለ​ኞ​ችሽ በሰ​ይፍ የቈ​ሰሉ አይ​ደ​ሉም፤ በአ​ንቺ ውስጥ የተ​ገ​ደ​ሉ​ትም በሰ​ልፍ የተ​ገ​ደሉ አይ​ደ​ሉም።


እነ​ዚ​ህም ደግሞ ከወ​ይን ጠጅ የተ​ነሣ ይስ​ታሉ፤ ከሚ​ያ​ሰ​ክ​ርም መጠጥ የተ​ነሣ አላ​ዋ​ቆች ይሆ​ናሉ፤ ካህ​ኑና ነቢዩ ከሚ​ያ​ሰ​ክር መጠጥ የተ​ነሣ ይስ​ታሉ፤ በወ​ይን ጠጅም ይዋ​ጣሉ፤ ከሚ​ያ​ሰ​ክ​ርም መጠጥ የተ​ነሣ ይበ​ድ​ላሉ፤ ይህም የዐ​ይን ምት​ሐት ነው፤ በፍ​ርድ ይሰ​ና​ከ​ላሉ።


ካህ​ና​ቱም፦ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወዴት አለ? አላ​ሉም፤ ሕጌን የተ​ማ​ሩ​ትም አላ​ወ​ቁ​ኝም፤ ጠባ​ቂ​ዎ​ችም ዐመ​ፁ​ብኝ፤ ነቢ​ያ​ትም በበ​ዐል ትን​ቢት ተና​ገሩ፤ የማ​ይ​ጠ​ቅ​ማ​ቸ​ው​ንም ነገር ተከ​ተሉ።


“እኔ ሳል​ል​ካ​ቸው እነ​ዚህ ነቢ​ያት ሮጡ፤ እኔም ሳል​ነ​ግ​ራ​ቸው ትን​ቢ​ትን ተና​ገሩ።


ነቢ​ያት በሐ​ሰት ትን​ቢት ይና​ገ​ራሉ፥ ካህ​ና​ትም በእ​ጃ​ቸው ያጨ​በ​ጭ​ባሉ፥ ሕዝ​ቤም እን​ዲህ ያለ​ውን ነገር ይወ​ድ​ዳሉ፤ በፍ​ጻ​ሜ​ውስ ምን ታደ​ር​ጋ​ላ​ችሁ?


ከታ​ናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ድረስ ሁሉ ኀጢ​አ​ትን አድ​ር​ገ​ዋ​ልና፥ ከሐ​ሳዊ ነቢይ ጀምሮ እስከ ካህኑ ድረስ ሁሉም ሐሰ​ትን አደ​ረጉ።


የጠ​ላት ሰይፍ ከብ​በ​ዋ​ች​ኋ​ልና ወደ ሜዳ አት​ውጡ፤ በመ​ን​ገ​ድም ላይ አት​ሂዱ።


ከታ​ናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ድረስ ሁሉ ስስ​ትን ያስ​ባ​ሉና፥ ከነ​ቢ​ዩም ጀምሮ እስከ ካህኑ ድረስ ሁሉ በተ​ን​ኰል ያደ​ር​ጋ​ሉና ስለ​ዚህ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ለሌ​ሎች፥ እር​ሻ​ቸ​ው​ንም ለሚ​ወ​ር​ሱ​ባ​ቸው እሰ​ጣ​ለሁ።


ሬስ። አቤቱ! ተጨ​ን​ቄ​አ​ለ​ሁና፥ አን​ጀ​ቴም ታው​ኮ​ብ​ኛ​ልና ተመ​ል​ከት፤ መራራ ኀዘን አዝ​ኛ​ለ​ሁና ልቤ በው​ስጤ ተገ​ላ​በ​ጠ​ብኝ፤ በሜዳ ሰይፍ አመ​ከ​ነ​ችኝ፤ በቤ​ትም ሞት አለ።


ቆፍ። ተነሺ፤ በሌ​ሊት በመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ሰዓት ጩኺ፥ በጌ​ታም ፊት ልብ​ሽን እንደ ውኃ አፍ​ስሺ፤ በጎ​ዳና ሁሉ ራስ ላይ በራብ ስለ ደከሙ ስለ ሕፃ​ና​ትሽ ነፍስ እጆ​ች​ሽን ወደ እርሱ አንሺ።


ጤት። በሰ​ይፍ የሞ​ቱት በራብ ከሞ​ቱት ይሻ​ላሉ፤ እነ​ዚህ የም​ድ​ርን ፍሬ አጥ​ተው ተወ​ግ​ተ​ውም ዐል​ፈ​ዋል።


ሰይፍ በውጭ፥ ቸነ​ፈ​ርና ራብ በው​ስጥ አለ፤ በሜዳ ያለው በሰ​ይፍ ይሞ​ታል፤ በከ​ተ​ማም ያለ​ውን ቸነ​ፈ​ርና ራብ ይፈ​ጁ​ታል።


“በከ​ተ​ማ​ችሁ ሁሉ ጥር​ስን ማጥ​ረ​ስን፥ በስ​ፍ​ራ​ች​ሁም ሁሉ እን​ጀ​ራን ማጣ​ትን ሰጠ​ኋ​ችሁ፤ እና​ንተ ግን ወደ እኔ አል​ተ​መ​ለ​ሳ​ች​ሁም ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


አለቆችዋ በጉቦ ይፈርዳሉ፥ ካህናቶችዋም በዋጋ ያስተምራሉ፥ ነቢያቶችዋም በገንዘብ ያምዋርታሉ፥ ከዚህም ጋር፦ እግዚአብሔር በመካከላችን አይደለምን? ክፉ ነገር ምንም አይመጣብንም እያሉ በእግዚአብሔር ይታመናሉ።


“እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አን​ተን፥ በአ​ን​ተም ላይ የም​ት​ሾ​ማ​ቸ​ውን አለ​ቆ​ች​ህን አን​ተና አባ​ቶ​ችህ ወዳ​ላ​ወ​ቃ​ች​ኋ​ቸው ሕዝብ ይወ​ስ​ድ​ሃል፤ በዚ​ያም ሌሎ​ችን የእ​ን​ጨ​ትና የድ​ን​ጋይ አማ​ል​ክ​ትን ታመ​ል​ካ​ለህ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ከም​ድር ዳር እስከ ዳር​ቻዋ ድረስ ወደ አሉ አሕ​ዛብ ሁሉ ይበ​ት​ን​ሃል፤ በዚ​ያም አን​ተና አባ​ቶ​ችህ ያላ​ወ​ቃ​ች​ኋ​ቸ​ውን ሌሎ​ችን አማ​ል​ክት፥ እን​ጨ​ት​ንና ድን​ጋ​ይን ታመ​ል​ካ​ለህ።


ገንዘብንም በመመኘት በተፈጠረ ነገር ይረቡባችኋል፤ ፍርዳቸውም ከጥንት ጀምሮ አይዘገይም፤ ጥፋታቸውም አያንቀላፋም።


ተከተሉን:

ማስታወቂያዎች


ማስታወቂያዎች