መሳፍንት 9:3 - መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)3 የእናቱ ዘመዶች ስለ እርሱ ሆነው እነዚህን ቃሎች ሁሉ ለሴኬም ነዋሪዎች በሙሉ ነገሩ፤ “እርሱማ ወንድማችን አይደል” ብለዋልና፥ አቤሜሌክንም ለመከተል ልባቸው ወደሱ አዘነበለ። ምዕራፉን ተመልከትአዲሱ መደበኛ ትርጒም3 የእናቱ ዘመዶች ስለ እርሱ ሆነው እነዚህን ቃሎች ሁሉ ለሴኬም ገዦች በሙሉ ነገሩ፤ አቢሜሌክንም ለመከተል ልባቸው ዳዳ፤ “እርሱማ ወንድማችን አይደል” ብለዋልና። ምዕራፉን ተመልከትአማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም3 የእናቱም ዘመዶች እርሱን ወክለው ይህንኑ ለሴኬም ሰዎች ነገሩአቸው፤ የሴኬም ሰዎችም እርሱ ወንድማችን ነው ብለው አቤሜሌክን የመከተል ፍላጎት አደረባቸው። ምዕራፉን ተመልከትየአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)3 የእናቱም ወንድሞች ይህን ቃል ሁሉ ስለ እርሱ በሰቂማ ሰዎች ሁሉ ጆሮ ተናገሩ፤ እነርሱም፥ “እርሱ ወንድማችን ነው” ብለው ልባቸውን ወደ አቤሜሌክ መለሱት። ምዕራፉን ተመልከትመጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)3 የእናቱም ወንድሞች ይህን ቃል ሁሉ ስለ እርሱ በሴኬም ሰዎች ሁሉ ጆሮ ተናገሩ፥ እነርሱም፦ እርሱ ወንድማችን ነው ብለው አቤሜሌክን ለመከተል ልባቸውን አዘነበሉት። ምዕራፉን ተመልከት |