本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明 መጽሐፈ ጦቢት 7:11 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)11 እኔም እውነቱን እነግርሃለሁ፤ ይህችን ልጄን ለሰባት ወንዶች አጋባኋት፤ ወደ እርሷም እንደ ገቡ በሌሊት ይሞታሉ፤ ነገር ግን አንድ ጊዜ ደስ ይበልህ፤” ጦብያም፥ “ነገሩን ለኔ እስክትጨርሱልኝ ድረስ፥ ነገሬንም እስክታጸኑልኝ ድረስ በዚህ ምንም አልቀምስም” አለ። 参见章节መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)11 ከዚህ ቀደም ከወገኖቻችን መካከል ከሰባት ሰዎች ጋር አጋብቻት ነበር፤ ሁሉም በመጀመሪያው ቀን ማታ ወደ ክፍሏ ሲገቡ ሞቱ። ለአሁን ግን ልጄ ብላ፥ ጠጣ፥ ጌታ ጸጋውንና ሰላሙን ይሰጥሃል።” ጦብያም “የእኔን ነገር እስክትወስንልኝ ምንም አልበላም፥ አልጠጣም” አለ። ራጉኤልም እንዲህ አለው “መልካም፤ በሙሴ መጽሐፍ መሠረት ለአንተ ተሰጥታለች፥ ለአንተ እንድትሰጥ ሰማይ እራሱ ደንግጓል፥ ስለዚህ እኀትህን ለአንተ ሰጥቻታለሁ፤ ከአሁን ጀምሮ ወንድሟ ነህ፥ እርሷም እኀትህ ናት። ከዛሬ ጀምሮ ለዘለዓለም ለአንተ ተሰጥለች። ልጄ የሰማዩ ጌታ በዚህች ሌሊት ሞገስ ይሁናችሁ፤ ጸጋውንና ሰላሙን ይስጣችሁ።” 参见章节 |