Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




ምሳሌ 14:28 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

28 የንጉሥ ክብር በሕዝብ ብዛት ነው፤ የገዥ ውድቀት ግን በሕዝብ ማነስ ነው።

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

28 የሕዝብ ብዛት የንጉሥ ክብር ሲሆን፣ የዜጎች ማነስ ግን ለገዥ መጥፊያው ነው።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

28 የንጉሥ ክብር በሕዝብ ብዛት ነው፥ በሰው ጥቂትነት ግን የገዥ ጥፋት አለ።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

28 የንጉሥ ታላቅነት የሚለካው በሚያስተዳድራቸው ሕዝብ ብዛት ነው፤ የሚገዛው ሕዝብ ከሌለው ግን ለንጉሡ ጥፋት ነው።

参见章节 复制




ምሳሌ 14:28
11 交叉引用  

አሁ​ንም ተነ​ሥ​ተህ ወጥ​ተህ ለአ​ገ​ል​ጋ​ዮ​ችህ በል​ባ​ቸው የሚ​ገባ ነገር ንገ​ራ​ቸው። ዛሬ ወደ እነ​ርሱ ካል​ወ​ጣህ በዚች ሌሊት አንድ ሰው ስንኳ ከአ​ንተ ጋር የሚ​ያ​ድር እን​ዳ​ይ​ኖር በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እም​ላ​ለሁ፤ ከሕ​ፃ​ን​ነ​ትህ ጀምሮ እስ​ከ​ዚች ቀን ድረስ ካገ​ኘህ መከራ ሁሉ ዛሬ የም​ታ​ገ​ኝህ መከራ እን​ድ​ት​ከ​ፋ​ብህ እን​ግ​ዲህ አንተ ለራ​ስህ ዕወቅ” አለው።


ኢዮ​አ​ብም ንጉ​ሡን፥ “የጌ​ታዬ የን​ጉሡ ዐይን እያየ አም​ላ​ክህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዛሬ ካለው ሕዝብ መጠን በላይ መቶ እጥፍ ይጨ​ም​ር​በት፤ ጌታዬ ንጉሡ ግን ይህን ነገር ለምን ይፈ​ል​ጋል?” አለው።


አክ​ዓ​ብም ይህን ቃል በሰማ ጊዜ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት የተ​ነሣ ደነ​ገጠ፤ ልብ​ሱ​ንም ቀደደ፤ እያ​ለ​ቀ​ሰም ሄደ፤ በሰ​ው​ነ​ቱም ላይ ማቅ ለበሰ፤ ጾመም፤ ኢይ​ዝ​ራ​ኤ​ላ​ዊው ናቡ​ቴ​ንም በገ​ደ​ለ​በት ቀን ደግሞ ማቅ ለብሶ ነበር።


ለኢ​ዮ​አ​ካ​ዝም ከኀ​ምሳ ፈረ​ሰ​ኞች፥ ከዐ​ሥ​ርም ሰረ​ገ​ሎች፥ ከዐ​ሥር ሺህም እግ​ረ​ኞች በቀር ሕዝብ አል​ቀ​ረ​ለ​ትም፤ የሶ​ርያ ንጉሥ አጥ​ፍ​ቶ​አ​ቸ​ዋ​ልና፥ በአ​ው​ድ​ማም እን​ዳለ ዕብቅ አድ​ቅ​ቆ​አ​ቸ​ዋ​ልና።


ነገር ግን እን​ዳ​ስ​ጨ​ነ​ቁ​አ​ቸው መጠን እን​ዲሁ በዙ፤ እጅ​ግም ጸኑ ፤ ግብ​ፃ​ው​ያ​ንም የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች ይጸ​የ​ፉ​አ​ቸው ነበር።


ፈር​ዖ​ንም፥ “የሚ​ወ​ለ​ደ​ውን ወንድ ልጅ ሁሉ ወደ ወንዝ ጣሉት፤ ሴትን ልጅ ሁሉ ግን በሕ​ይ​ወት አድ​ኑ​አት” ብሎ ሕዝ​ቡን ሁሉ አዘዘ።


የእግዚአብሔር ትእዛዝ የሕይወት ምንጭ ነው። ሰዎችንም ከሞት ወጥመድ እንዲያመልጡ ያደርጋል።


ትዕግሥተኛ ሰው ጥበብ የበዛለት ይሆናል፤ ትዕግሥት የጐደለው ሰው ግን ሰነፍ ነው፤


ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሆይ! ዐይ​ን​ሽን አን​ሥ​ተሽ እነ​ዚ​ህን ከሰ​ሜን የሚ​መ​ጡ​ትን ተመ​ል​ከቺ፤ ለአ​ንቺ የሰ​ጠ​ሁሽ መንጋ፤ የክ​ብር በጎ​ችሽ ወዴት አሉ?


跟着我们:

广告


广告