Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




ዘኍል 21:24 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

24 እስ​ራ​ኤ​ልም በሰ​ይፍ መታው፤ ምድ​ሩ​ንም ከአ​ር​ኖን ጀምሮ እስከ አሞን ልጆች እስከ ያቦቅ ድረስ ወረሰ፤ የአ​ሞ​ንም ልጆች ዳርቻ ኢያ​ዜር ነበረ።

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

24 እስራኤል ግን በሰይፍ መታው፤ ከአርኖን እስከ ያቦቅ ድረስ ያለውንም ምድሩን ወሰደበት፤ ይሁን እንጂ የአሞናውያን ወሰን የተመሸገ ስለ ነበር ከያቦቅ አላለፈም።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

24 እስራኤልም በሰይፍ መታው፥ ምድሩንም ከአርኖን ጀምሮ እስከ ያቦቅ እስከ አሞን ልጆች ድረስ ወረሰ፤ የአሞንም ልጆች ዳርቻ የጸና ነበረ።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

24 እስራኤላውያን ግን ድል ነሡአቸው፤ ከአርኖን ወንዝ አንሥቶ በስተሰሜን እስከ ዐሞናውያን ወሰን ማለትም እስከ ያቦቅ ወንዝ ድረስ የሚገኘውን ግዛት ያዙ፤ ይሁን እንጂ የዐሞናውያን ወሰን በብርቱ የተጠበቀ በመሆኑ ወደዚያ አልገቡም።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

24 እስራኤልም በሰይፍ መታው፥ ምድሩንም ከአሮኖን ጀምሮ እስከ አሞን ልጆች እስከ ያቦቅ ድረስ ወረሰ፤ የአሞንም ልጆች ዳርቻ የጸና ነበረ።

参见章节 复制




ዘኍል 21:24
24 交叉引用  

በዚ​ያ​ችም ሌሊት ተነሣ፥ ሁለ​ቱን ሚስ​ቶ​ቹ​ንና ሁለ​ቱን ዕቁ​ባ​ቶ​ቹን ዐሥራ አን​ዱ​ንም ልጆ​ቹን ይዞ የያ​ቦ​ቅን ወንዝ ተሻ​ገረ።


“መን​ግ​ሥ​ታ​ት​ንና አሕ​ዛ​ብን ዕድል ፈንታ አድ​ር​ገህ ሰጠ​ሃ​ቸው፤ የሐ​ሴ​ቦ​ንን ንጉሥ የሴ​ዎ​ንን ምድር፥ የባ​ሳ​ን​ንም ንጉሥ የዐ​ግን ምድር ወረሱ።


እኔ ግን ቁመቱ እንደ ዝግባ ቁመት፥ ብር​ታ​ቱም እንደ ወይራ ዛፍ የነ​በ​ረ​ውን አሞ​ራ​ዊ​ውን ከፊ​ታ​ቸው አጠ​ፋሁ፤ ፍሬ​ው​ንም ከላዩ፥ ሥሩ​ንም ከታቹ አጠ​ፋሁ።


ከዚ​ያም ተጕ​ዘው ከአ​ሞ​ራ​ው​ያን ዳርቻ በሚ​ወ​ጣው ምድረ በዳ ውስጥ በአ​ር​ኖን ማዶ ሰፈሩ፤ አር​ኖን በሞ​ዓ​ብና በአ​ሞ​ራ​ው​ያን መካ​ከል ያለ የሞ​ዓብ ዳርቻ ነውና።


በሐ​ሴ​ቦን ተቀ​ምጦ የነ​በ​ረ​ውን የአ​ሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያ​ንን ንጉሥ ሴዎ​ንን፥ በአ​ስ​ጣ​ሮ​ትና በኤ​ድ​ራ​ይን ተቀ​ምጦ የነ​በ​ረ​ው​ንም የባ​ሳ​ንን ንጉሥ ዐግን ከገ​ደ​ሉት በኋላ፥


የሐ​ሴ​ቦን ንጉሥ ሴዎን፥ የባ​ሳ​ንም ንጉሥ ዐግ ሊወ​ጉን ወጡ​ብን፤ እኛም መታ​ና​ቸው፤


ለሮ​ቤ​ልና ለጋ​ድም ከገ​ለ​ዓድ ምድር ጀምሮ እስከ አር​ኖን ሸለቆ ድረስ የሸ​ለ​ቆ​ውን እኩ​ሌታ ዳር​ቻ​ው​ንም፥ እስከ አሞን ልጆች ዳርቻ እስከ ኢያ​ቦቅ ወንዝ ድረስ፥


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ክም ባጠ​ፋ​ቸው በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ በሚ​ኖሩ በሁ​ለቱ በአ​ሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያን ነገ​ሥ​ታት በሴ​ዎ​ንና በዐግ፥ በም​ድ​ራ​ቸ​ውም እን​ዳ​ደ​ረገ እን​ዲሁ ያደ​ር​ግ​ባ​ቸ​ዋል።


ሙሴና የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ከግ​ብፅ ከወጡ በኋላ በመ​ቱት፥ በሐ​ሴ​ቦን ተቀ​ምጦ በነ​በ​ረው በአ​ሞ​ሬ​ዎን ንጉሥ በሴ​ዎን ምድር፥ በቤተ ፌጎር አቅ​ራ​ቢያ ባለው ሸለቆ በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ፤


በባ​ሳን የነ​በ​ረ​ውን፥ በአ​ስ​ታ​ሮ​ትና በኤ​ን​ድ​ራ​ይን የነ​ገ​ሠ​ውን የዐ​ግን መን​ግ​ሥት ሁሉ፤ እር​ሱም ከረ​ዓ​ይት የቀረ ነበረ፤ እነ​ዚ​ህ​ንም ሙሴ አወ​ጣ​ቸው፤ ገደ​ላ​ቸ​ውም።


በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶ ወደ ተቀ​መ​ጡት ወደ አሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያን ምድ​ርም ወሰ​ድ​ኋ​ችሁ፤ ከእ​ና​ን​ተም ጋር ተዋጉ፤ ሙሴም ተዋ​ጋ​ቸው፤ አሳ​ል​ፌም በእ​ጃ​ችሁ ሰጠ​ኋ​ችሁ፤ ምድ​ራ​ቸ​ው​ንም ወረ​ሳ​ችሁ፤ ከፊ​ታ​ች​ሁም አጠ​ፋ​ኋ​ቸው።


በዮ​ር​ዳ​ኖስ ማዶም በነ​በ​ሩት በሁ​ለቱ በአ​ሞ​ሬ​ዎን ነገ​ሥት በሐ​ሴ​ቦን ንጉሥ በሴ​ዎን፥ በአ​ስ​ታ​ሮ​ትና በኤ​ድ​ራ​ይን በነ​በ​ረው በባ​ሳን ንጉሥ በዐግ ያደ​ረ​ገ​ውን ሁሉ ሰም​ተ​ናል።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች አላ​ቸው፥ “ግብ​ፃ​ው​ያን፥ አሞ​ሬ​ዎ​ና​ው​ያ​ንም፥ የአ​ሞ​ንና የሞ​አ​ብም ልጆች፥ ፍል​ስ​ጥ​ኤ​ማ​ው​ያ​ንም፥


የአ​ሞ​ንም ልጆች ንጉሥ የዮ​ፍ​ታ​ሔን መል​እ​ክ​ተ​ኞች፥ “እስ​ራ​ኤል ከግ​ብፅ በወጣ ጊዜ ከአ​ር​ኖን ጀምሮ እስከ ያቦ​ቅና እስከ ዮር​ዳ​ኖስ ድረስ ምድ​ሬን ስለ ወሰደ ነው፤ አሁ​ንም በሰ​ላም መል​ሱ​ልኝ” ብሎ መለ​ሰ​ላ​ቸው።


እነ​ር​ሱም፥ “ከእ​ስ​ራ​ኤል ነገድ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ወደ መሴፋ ያል​ወጣ ማን ነው?” አሉ። እነ​ሆም፥ ከኢ​ያ​ቢስ ገለ​ዓድ ወደ ሰፈሩ ወደ ጉባ​ኤው ማንም አል​ወ​ጣም ነበር።


跟着我们:

广告


广告