8 ፈጽሞ ያልበደለ፥ ግፍን ከሚሠሩም ጋር ያልተባበረ፥ ከኃጥኣንም ጋር ያልሄደ፥ ማን ነው?
8 ከክፉ አድራጊዎች ጋራ ይተባበራል፤ ከኀጢአተኞችም ጋራ ግንባር ይፈጥራል።
8 ጓደኞቹ ክፉ አድራጊዎች ናቸው፤ የሚውለውም ከክፉ አድራጊዎች ጋር ነው።
ንግግር አታብዛ፤ የሚከራከርህ የለምና።
ከአፍህ ንግግር የተነሣ መጠንህ ይታወቃል፥ የኀያላኑንም ቃል አልለየህም።
እርሱ ግን፦ ወደ እርስዋ ተመለከተና እንዲህ አላት፥ “አንቺ ከሰነፎች ሴቶች እንደ አንዲቱ ተናገርሽ፤ ከእግዚአብሔር እጅ መልካሙን ተቀበልን፥ ክፉውን ነገርስ አንታገሥምን?” በዚህ በደረሰበት ሁሉ ኢዮብ በእግዚአብሔር ፊት በከንፈሩ አልበደለም።
በውኑ ጻድቃን ሰዎች የረገጡአትን የዱሮይቱን መንገድ ትጠብቃለህን?
ሰው ከእግዚአብሔር ጕብኝት ሲኖረው እግዚአብሔር አይጐበኘውም አትበል።
ምስጉን ነው፥ በዝንጉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኀጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ ሰው።
እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት፥ እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ በቤተ መቅደሱም አገለግል ዘንድ።
አቤቱ፥ በውዴታህ ጽዮንን አሰማምራት፤ የኢየሩሳሌምም ቅጽሮች ይታነጹ።
ልጄ ሆይ፥ ከእነርሱ ጋር በመንገድ አትሂድ፥ ከጎዳናቸውም እግርህን ፈቀቅ አድርግ፤
ከጠቢባን ጋር የሚሄድ ጠቢብ ይሆናል፤ ከአላዋቂዎች ጋር የሚሄድ ግን አላዋቂ ይሆናል።
አንተን ከክፉ መንገድ፥ ምንም የሚታመን ነገርን ከማይናገር ሰውም ታድንህ ዘንድ፥
በክፉዎች መንገድ አትሂድ፥ በክፉ ሰዎችም ጎዳና አትቅና።
ወንድሞቻችን አያስቱአችሁ፤ ክፉ ነገር መልካም ጠባይን ያበላሻልና።