Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




ኢሳይያስ 49:20 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

20 አጥ​ተ​ሻ​ቸው የነ​በ​ሩት ልጆ​ች​ሽም በጆ​ሮሽ፦ ስፍራ ጠብ​ቦ​ና​ልና የም​ን​ቀ​መ​ጥ​በት ቦታ አስ​ፊ​ልን ይላሉ።

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

20 በሐዘንሽ ዘመን የወለድሻቸው ልጆች፣ ጆሮሽ እየሰማ፣ ‘ይህ ቦታ በጣም ጠብቦናል፤ የምንኖርበት በቂ ስፍራ ስጪን’ ይሉሻል።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

20 የወላድ መካን ከሆንሽ በኋላ የተወለዱልሽ ልጆችሽ በጆሮሽ፦ “ስፍራ ጠብቦኛልና እድንቀመጥ ቦታ አስፊልን” ይላሉ።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

20 በስደት የተወለዱ ልጆችሽ ‘ይህ ቦታ ለእኛ በጣም ጠባብ ስለ ሆነ የምንኖርበት ሰፊ ቦታ ስጪን’ ይሉሻል።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

20 የወላድ መካን ከሆንሽ በኋላ የተወለዱልሽ ልጆችሽ በጆሮሽ፦ ስፍራ ጠብቦኛልና እቀመጥ ዘንድ ቦታ አስፊልኝ ይላሉ።

参见章节 复制




ኢሳይያስ 49:20
11 交叉引用  

የነ​ቢ​ያ​ትም ልጆች ኤል​ሳ​ዕን፥ “እነሆ፥ በፊ​ትህ የም​ና​ድ​ር​በት ቤት ጠብ​ቦ​ናል።


ነገር ግን ልጆ​ቻ​ቸው የእ​ጄን ሥራ ባዩ ጊዜ ስለ እኔ ስሜን ይቀ​ድ​ሳሉ፤ የያ​ዕ​ቆ​ብ​ንም ቅዱስ ይቀ​ድ​ሳሉ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም አም​ላክ ይፈ​ራሉ።


ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ሆይ፥ ደስ አሰ​ኝ​ሻ​ለሁ፤ ባድ​ማ​ሽ​ንም ሁሉ ደስ አሰ​ኛ​ለሁ፤ ምድረ በዳ​ሽ​ንም እንደ ዔድን፥ በረ​ሃ​ዎ​ች​ሽ​ንም እንደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ገነት አደ​ር​ጋ​ለሁ። ደስ​ታና ተድላ እም​ነ​ትና የዝ​ማሬ ድምፅ በው​ስጧ ይገ​ኝ​ባ​ታል።


ዐይ​ኖ​ች​ሽን አን​ሥ​ተሽ በዙ​ሪ​ያሽ ተመ​ል​ከቺ፤ ልጆ​ች​ሽም እንደ ተሰ​በ​ሰቡ እነሆ፥ እዪ፤ ወን​ዶች ልጆ​ችሽ ከሩቅ ይመ​ጣሉ፤ ሴቶች ልጆ​ች​ሽ​ንም በጫ​ንቃ ላይ ይሸ​ከ​ሙ​አ​ቸ​ዋል።


የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ቍጥር እን​ደ​ማ​ይ​ሰ​ፈ​ርና እን​ደ​ማ​ይ​ቈ​ጠር እንደ ባሕር አሸዋ ይሆ​ናል፤ እን​ዲ​ህም ይሆ​ናል፤ “እና​ንተ ሕዝቤ አይ​ደ​ላ​ች​ሁም” ተብሎ በተ​ነ​ገ​ረ​በት በዚያ ስፍራ የሕ​ያው አም​ላክ ልጆች ይባ​ላሉ።


ከግብጽም ምድር እመልሳቸዋለሁ፥ ከአሦርም እሰበስባቸዋለሁ፣ ወደ ገለዓድና ወደ ሊባኖስ ምድር አመጣቸዋለሁ፥ የሚበቃም ቦታ አይገኝላቸውም።


ሩጥ፥ ይህንም ጕልማሳ እንዲህ በለው፦ ኢየሩሳሌም በውስጥዋ ካሉት ሰዎችና እንስሶች ብዛት የተነሣ ቅጥር እንደሌላቸው መንደሮች ሆና ትኖራለች።


በልባችሁም ‘አብርሃም አባት አለን’ እንደምትሉ አይምሰላችሁ፤ እላችኋለሁና ከነዚህ ድንጋዮች ለአብርሃም ልጆች ሊያስነሣለት እግዚአብሔር ይችላል።


跟着我们:

广告


广告