Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




ኢሳይያስ 27:10 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

10 በዚ​ያም የተ​ሰ​ማ​ራው መንጋ እንደ ተተወ መንጋ ይሆ​ናል፤ ምድ​ሩም ለብዙ ዘመን መሰ​ማ​ሪያ ይሆ​ናል፤ በዚ​ያም መን​ጋው ይሰ​ማ​ራል፤ ያር​ፋ​ልም።

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

10 የተመሸገባት ከተማ ባዶዋን ቀርታለች፤ እንደ ምድረ በዳም የተተወች ስፍራ ሆናለች፤ ጥጆች በዚያ ይሰማራሉ፤ እዚያም ይተኛሉ፤ ቅርንጫፎቿንም ልጠው ይበላሉ።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

10 የተመሸገችው ከተማ ብቻዋን ሆነች፤ እንደ ምድረ በዳ ሆና የተተወች መኖሪያ ሆናለች፤ በዚያም ጥጃ ይሰማራል፥ በዚያም ይተኛል ቅርንጫፍዋንም ይበላል።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

10 የተመሸገችው ከተማ ፈራርሳለች፤ ባዶዋን ቀርታ ጭው ያለ ምድረ በዳ መስላለች፤ የከብቶች መሰማሪያ ስለ ሆነች በዚያ ጥጆች የዛፍ ቅርንጫፎችን እየበሉ ያርፋሉ።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

10 የተመሸገችው ከተማ ብቻዋን ሆነች፥ እንደ ምድረ በዳ ሆና የተፈታችና የተተወች መኖሪያ ናት፥ በዚያም ጥጃ ይሰማራል በዚያም ይተኛል ቅርንጫፍዋንም ይበላል።

参见章节 复制




ኢሳይያስ 27:10
24 交叉引用  

ለዘ​ለ​ዓ​ለም የተ​ፈ​ታች ትሆ​ና​ለች፤ ለመ​ንጋ ማሰ​ማ​ር​ያም ትሆ​ና​ለች፤ የሚ​ያ​ሳ​ድ​ዳ​ቸ​ውም የለም።


በዚ​ያም ቀን በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ፊት የአ​ሞ​ራ​ው​ያ​ንና የኤ​ዌ​ዎ​ያ​ው​ያን ከተ​ሞች እንደ ተፈቱ፥ እን​ዲሁ ከተ​ሞ​ችህ ይፈ​ታሉ፤ ባድ​ማም ይሆ​ናሉ።


ከተ​ሞች ሁሉ ምድረ በዳ ሆኑ፤ ቤቶ​ችም ሁሉ ማንም እን​ዳ​ይ​ገ​ባ​ባ​ቸው ተዘጉ።


ከተ​ሞ​ችን ትቢያ አደ​ረ​ግህ፤ የተ​መ​ሸጉ ከተ​ሞ​ችን፥ የኃ​ጥ​ኣ​ን​ንም መሠ​ረት አፈ​ረ​ስህ፤ ከተ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ለዘ​ለ​ዓ​ለም አይ​ሠ​ሩም።


በረዶ ቢወ​ርድ አይ​ደ​ር​ስ​ባ​ች​ሁም፤ በዛፍ ሥር የሚ​ኖሩ ሰዎች በበ​ረሃ እን​ደ​ሚ​ኖሩ ሰዎች ታም​ነው ይኖ​ራሉ።


የተ​ጠ​ማው ምድረ በዳ ደስ ይለ​ዋል፤ በረ​ሃ​ውም ሐሤት ያደ​ር​ጋል፤ እንደ ጽጌ​ረ​ዳም ያብ​ባል።


አን​ቺም በል​ብሽ፦ የወ​ላድ መካን ሆኛ​ለ​ሁና፥ እኔም መበ​ለት ነኝና እነ​ዚ​ህን ማን ወለ​ደ​ልኝ? እነ​ዚ​ህ​ንስ ማን አሳ​ደ​ጋ​ቸው? እነሆ፥ ብቻ​ዬን ቀርቼ ነበር፤ እነ​ዚ​ህስ ከወ​ዴት መጡ?” ትያ​ለሽ።


የተ​ቀ​ደሱ ከተ​ሞ​ችህ ምድረ በዳ ሆነ​ዋል፤ ጽዮን ምድረ በዳ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ውድማ ሆና​ለች።


በዚ​ያም ቀን እን​ዲህ ይሆ​ናል፤ ሰው ከላ​ሞቹ አን​ዲት ጊደ​ር​ንና ሁለት በጎ​ችን ያሳ​ድ​ጋል፤ የአ​ን​ዲት በግ ወተ​ትም ሁለት ሰዎ​ችን ያጠ​ግ​ባል።


በሚ​ታ​ረ​ሰ​ውም ተራራ ሁሉ ላይ ፍር​ሀት ይመ​ጣል፤ የበ​ጎች መሰ​ማ​ርያ ይሆ​ናል፤ በሬ​ዎ​ችም ይረ​ግ​ጡ​ታል፤ እሾ​ህና ኵር​ን​ች​ትም ያጠ​ፋ​ዋል።


ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጽኑ ቍጣ የተ​ነሣ የሰ​ላም ውበት ፈር​ሶ​አል።


“ሞሬ​ታ​ዊው ሚክ​ያስ በይ​ሁዳ ንጉሥ በሕ​ዝ​ቅ​ያስ ዘመን ትን​ቢት ይና​ገር ነበር፤ ለይ​ሁ​ዳም ሕዝብ ሁሉ፦ የሠ​ራ​ዊት ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ ጽዮን እንደ እርሻ ትታ​ረ​ሳ​ለች፤ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ምድረ በዳ ትሆ​ና​ለች፤ የቤ​ቱም ተራራ እንደ ዱር ከፍታ ይሆ​ናል ብሎ ተና​ገረ።


ይህን ቤት እንደ ሴሎ አደ​ር​ገ​ዋ​ለሁ፤ ይች​ንም ከተማ ለም​ድር አሕ​ዛብ ሁሉ ርግ​ማን አደ​ር​ጋ​ታ​ለሁ።”


የባ​ቢ​ሎ​ንም ንጉሥ መታ​ቸው፤ በኤ​ማ​ትም ምድር ባለ​ችው በዴ​ብ​ላታ ገደ​ላ​ቸው፤ እን​ዲሁ ይሁዳ ከሀ​ገሩ ተማ​ረከ።


ዳሌጥ። ወደ ዓመት በዓል የሚ​መጣ የለ​ምና የጽ​ዮን መን​ገ​ዶች አለ​ቀሱ፤ በሮ​ችዋ ሁሉ ፈር​ሰ​ዋል፤ ካህ​ና​ቷም ያለ​ቅ​ሳሉ፤ ደና​ግ​ሎ​ች​ዋም ተማ​ረኩ፤ እር​ስ​ዋም በም​ሬት አለች።


የጽ​ዮን ተራራ ባድማ ሆና​ለ​ችና፥ ቀበ​ሮ​ዎ​ችም ተመ​ላ​ል​ሰ​ው​ባ​ታ​ልና።


ስለ​ዚህ፥ እና​ንተ የእ​ስ​ራ​ኤል ተራ​ሮች ሆይ! የጌታ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቃል ስሙ። ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለተ​ራ​ሮ​ችና ለኮ​ረ​ብ​ቶች፥ ለፈ​ሳ​ሾ​ችና ለሸ​ለ​ቆ​ዎች፥ ለም​ድረ በዳ​ዎች፥ ባዶ ለሆ​ኑ​ትና ለፈ​ረ​ሱት፥ በዙ​ሪያ ላሉት ለቀ​ሩት አሕ​ዛብ ምር​ኮና መሣ​ለ​ቂያ ለሆ​ኑት ከተ​ሞች እን​ዲህ ይላል፦


ስለዚህ በእናንተ ምክንያት ጽዮን እንደ እርሻ ትታረሳለች፥ ኢየሩሳሌም የድንጋይ ክምር ትሆናለች፥ የቤቱም ተራራ እንደ ዱር ከፍታ ይሆናል።


跟着我们:

广告


广告