Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




ሕዝቅኤል 14:21 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

21 ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም እን​ዲህ ይላል፥ “ይል​ቁ​ንስ ሰው​ንና እን​ስ​ሳን ከእ​ር​ስዋ አጠፋ ዘንድ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ላይ አራ​ቱን ክፉ መቅ​ሠ​ፍ​ቶ​ችን፥ ሰይ​ፍ​ንና ራብን፥ ክፉ​ዎ​ች​ንም አው​ሬ​ዎች፥ ቸነ​ፈ​ር​ንም ስሰ​ድ​ድ​ባት፥

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

21 “ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፤ ‘ሰውንና እንስሳቱን ለማጥፋት አራቱን አስፈሪ ፍርዶቼን፦ ሰይፍን፣ ራብን፣ የዱር አራዊትንና ቸነፈርን በኢየሩሳሌም ላይ በማመጣበት ጊዜ ምንኛ የከፋ ይሆን!

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

21 ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በኢየሩሳሌም ላይ አራቱን ክፉ ፍርዶቼን ሰይፍ፥ ራብ፥ ክፉ አውሬና ቸነፈር፥ ሰውንና እንስሳን ከእርሷ ለማጥፋት ብሰድድም፥

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

21 ልዑል እግዚአብሔር የሚለው ይህ ነው፦ “ሕዝብንና እንስሶችን በአንድነት ለመጨረስ ጦርነትን፥ ራብን፥ አራዊትንና ቸነፈርን እነዚህን እጅግ የከፉ አራት መቅሠፍቶች በኢየሩሳሌም ላይ አመጣለሁ።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

21 ጌታ እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል፦ ይልቁንስ ሰውንና እንስሳን ከእርስዋ አጠፋ ዘንድ በኢየሩሳሌም ላይ አራቱን ክፉ ፍርዶቼን፥ ሰይፍንና ራብን ክፉዎችንም አውሬዎች ቸነፈርንም፥ ስሰድድባት!

参见章节 复制




ሕዝቅኤል 14:21
18 交叉引用  

ጋድም ወደ ዳዊት መጥቶ፥ “የሦ​ስት ዓመት ራብ በሀ​ገ​ርህ ላይ ይም​ጣ​ብ​ህን? ወይስ ጠላ​ቶ​ችህ እያ​ሳ​ደ​ዱህ ሦስት ወር ከእ​ነ​ርሱ ትሸ​ሽን? ወይስ የሦ​ስት ቀን ቸነ​ፈር በሀ​ገ​ርህ ላይ ይሁን? የሚ​ሻ​ል​ህን ምረጥ። አሁ​ንም ለላ​ከኝ ምን መልስ እን​ደ​ም​ሰጥ አስ​ብና መር​ምር” ብሎ ነገ​ረው።


አሁ​ንም እነ​ዚህ ሁለቱ ይጠ​ብ​ቁ​ሻል፤ ማን ያስ​ተ​ዛ​ዝ​ን​ሻል? እነ​ር​ሱም ጥፋ​ትና ውድ​ቀት ራብና ሰይፍ ናቸው፤ እን​ግ​ዲህ የሚ​ያ​ጽ​ና​ናሽ ማን ነው?


“ለባ​ቢ​ሎን ንጉ​ሥም ለና​ቡ​ከ​ን​ደ​ነ​ፆር የማ​ይ​ገ​ዛ​ውን፥ ከባ​ቢ​ሎ​ንም ንጉሥ ቀን​በር በታች አን​ገ​ቱን ዝቅ የማ​ያ​ደ​ር​ገ​ውን ሕዝ​ብና መን​ግ​ሥት፥ ያን ሕዝብ በእጁ እስ​ካ​ጠ​ፋው ድረስ በሰ​ይ​ፍና በራብ፥ በቸ​ነ​ፈ​ርም እቀ​ጣ​ለሁ፥ ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


አሕ​ዛ​ብም መጥ​ተው ይህ​ችን ሀገር ያዟት፤ ይህ​ችም ከተማ ከረ​ኃ​ቡና ከጦሩ የተ​ነሣ በወ​ጓት በከ​ለ​ዳ​ው​ያን ሰዎች እጅ ወደ​ቀች፤ እንደ ተና​ገ​ር​ኸ​ውም ሆነ።


በሚ​ሄ​ዱ​ባ​ቸ​ውም አሕ​ዛብ መካ​ከል ርኵ​ሰ​ታ​ቸ​ውን ሁሉ ይና​ገሩ ዘንድ ከሰ​ይ​ፍና ከራብ፥ ከቸ​ነ​ፈ​ርም ጥቂ​ቶች ሰዎ​ችን ከእ​ነ​ርሱ አስ​ቀ​ራ​ለሁ፤ እኔም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሆንሁ ያው​ቃሉ።”


“የሰው ልጅ ሆይ! ምድር ብት​በ​ድ​ለኝ፥ ብት​ስት፥ ኀጢ​አ​ትም ብት​ሠራ እጄን በእ​ር​ስዋ አነ​ሣ​ለሁ፤ የእ​ህ​ሉ​ንም ኀይል አጠ​ፋ​ለሁ፤ በእ​ር​ስ​ዋም ረሀ​ብን እል​ካ​ለሁ፤ ከብ​ቱ​ንና ሰዉ​ንም ከእ​ር​ስዋ አጠ​ፋ​ለሁ።


በዚ​ያች ሀገር ላይ ክፉ አው​ሬን ባመጣ፥ ፈጽ​ሜም ባጠ​ፋት በዚ​ያም አውሬ ፊት የሚ​ያ​ልፍ ባይ​ገኝ፥


ወይም በዚ​ያች ምድር ላይ ሰይፍ አም​ጥቼ፦ ሰይፍ ሆይ! በም​ድ​ሪቱ ላይ እለፊ ብል፥ ሰው​ንና እን​ስ​ሳ​ው​ንም ከእ​ር​ስዋ ባጠፋ፥


ወይም በዚ​ያች ምድር ላይ ቸነ​ፈ​ርን ብሰ​ድድ፥ ሰው​ንና እን​ስ​ሳ​ው​ንም ከእ​ር​ስዋ አጠፋ ዘንድ መዓ​ቴን በደም ባፈ​ስ​ስ​ባት፥


ኖኅና ዳን​ኤል ኢዮ​ብም በመ​ካ​ከ​ልዋ ቢኖሩ፤ እኔ ሕያው ነኝ! በጽ​ድ​ቃ​ቸው ነፍ​ሳ​ቸ​ውን ብቻ ያድ​ናሉ እንጂ ወን​ዶ​ች​ንና ሴቶች ልጆ​ቻ​ቸ​ውን አያ​ድ​ኑም፥” ይላል ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


ጌታ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ እኔ ሕያው ነኝና በባ​ድማ ስፍ​ራ​ዎች ያሉ በሰ​ይፍ ይወ​ድ​ቃሉ፤ በም​ድረ በዳ ያለ​ውን ለአ​ራ​ዊት መብል አድ​ርጌ እሰ​ጣ​ለሁ፤ በአ​ም​ባ​ዎ​ችና በዋ​ሻ​ዎች ያሉ በቸ​ነ​ፈር ይሞ​ታሉ።


ከአ​ን​ቺም ሢሶው በቸ​ነ​ፈር ይሞ​ታል፤ በመ​ካ​ከ​ል​ሽም በራብ ያል​ቃል፤ ሢሶ​ውም በዙ​ሪ​ያሽ በሰ​ይፍ ይወ​ድ​ቃል፤ ሢሶ​ው​ንም ወደ ነፋ​ሳት ሁሉ እበ​ት​ና​ለሁ፤ በኋ​ላ​ቸ​ውም ሰይ​ፍን እመ​ዝ​ዛ​ለሁ።


“ቍጣ​ዬ​ንና መዓ​ቴ​ንም በእ​ነ​ርሱ ላይ እጨ​ር​ሳ​ለሁ፤ መዓ​ቴ​ንም በፈ​ጸ​ም​ሁ​ባ​ቸው ጊዜ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቅ​ን​ዓቴ እንደ ተና​ገ​ርሁ ታው​ቂ​ያ​ለሽ።


ራብ​ንና ክፉ​ዎ​ችን አራ​ዊት እሰ​ድ​ድ​ብ​ሻ​ለሁ፤ እቀ​ሥ​ፍ​ሻ​ለሁ፤ ልጆ​ች​ሽ​ንም ያጠ​ፋሉ ቸነ​ፈ​ርና ደምም በአ​ንቺ ላይ ይመ​ጡ​ብ​ሻል፤ ሰይ​ፍ​ንም አመ​ጣ​ብ​ሻ​ለሁ፤ ይከ​ቡ​ሻ​ልም። እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይህን ተና​ግ​ሬ​አ​ለሁ።”


跟着我们:

广告


广告