Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




2 ነገሥት 23:6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

6 የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ድ​ንም ጣዖት ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌም ውጭ ወደ ቄድ​ሮን ፈፋ አወ​ጣው፤ በቄ​ድ​ሮ​ንም ፈፋ አጠ​ገብ አቃ​ጠ​ለው፤ አድ​ቅ​ቆም ትቢያ አደ​ረ​ገው፥ ትቢ​ያ​ው​ንም በሕ​ዝብ መቃ​ብር ላይ ጨመ​ረው።

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

6 የአሼራንም ምስል ዐምድ ከእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ አውጥቶ ከኢየሩሳሌም ውጭ ወዳለው ወደ ቄድሮን ሸለቆ ወስዶ አቃጠለው፤ አድቅቆ ፈጭቶም በሕዝቡ መቃብር ላይ በተነው።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

6 አሼራ ተብላ የምትጠራውን ሴት አምላክ ምስል ከቤተ መቅደስ ነቅሎ ከከተማይቱ በማውጣት ወደ ቄድሮን ሸለቆ ወስዶ በእሳት አቃጠለው፤ ትቢያ እስኪሆንም አድቅቆ፥ በሕዝብ መቃብር ላይ በተነው።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

6 አሼራ ተብላ የምትጠራውን ሴት አምላክ ምስል ከቤተ መቅደስ ነቅሎ ከከተማይቱ በማውጣት ወደ ቄድሮን ሸለቆ ወስዶ በእሳት አቃጠለው፤ ትቢያ እስኪሆንም አድቅቆ፥ በሕዝብ መቃብር ላይ በተነው።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

6 የማምለኪያ ዐፀድንም ጣዖት ከእግዚአብሔር ቤት ወደ ኢየሩሳሌም ውጭ ወደ ቄድሮን ፈፋ አወጣው፤ በቄድሮንም ፈፋ አጠገብ አቃጠለው፤ አድቅቆም ትቢያ አደረገው፤ ትቢያውንም በሕዝብ መቃብር ላይ ጣለው።

参见章节 复制




2 ነገሥት 23:6
20 交叉引用  

እነ​ር​ሱም ደግሞ ከፍ ባለው ኮረ​ብታ ሁሉ ላይ፥ ቅጠ​ሉም ከለ​መ​ለመ ዛፍ ሁሉ በታች መስ​ገ​ጃ​ዎ​ችን ሠሩ፤ ሐው​ል​ቶ​ች​ንና የማ​ም​ለ​ኪያ አፀ​ዶ​ች​ንም ለራ​ሳ​ቸው አቆሙ።


የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀድ ጣዖ​ታ​ትን ስለ ሠራች እና​ቱን ሐናን እቴጌ እን​ዳ​ት​ሆን ሻራት፤ አሳም የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ዱን አስ​ቈ​ረ​ጠው፥ በቄ​ድ​ሮ​ንም ፈፋ አጠ​ገብ በእ​ሳት አቃ​ጠ​ለው።


አክ​ዓ​ብም የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ድን አሠራ፤ አክ​ዓ​ብም ሰው​ነቱ እን​ድ​ት​ጠፋ ከእ​ርሱ በፊት ከነ​በ​ሩት ከእ​ስ​ራ​ኤል ነገ​ሥ​ታት ሁሉ ይልቅ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ያ​ስ​ቈ​ጣ​ውን ነገር አበዛ።


በም​ት​ወ​ጣ​በ​ትና የቄ​ድ​ሮ​ን​ንም ፈፋ በም​ት​ሻ​ገ​ር​በት ቀን ፈጽ​መህ እን​ደ​ም​ት​ሞት ዕወቅ፤ ደም​ህም በራ​ስህ ላይ ይሆ​ናል።” ያን​ጊ​ዜም ንጉሡ አማ​ለው።


ከበ​ዓ​ልም ቤት ሐው​ል​ቶ​ቹን አወጡ፤ አቃ​ጠ​ሉ​አ​ቸ​ውም።


የበ​ዓ​ልን ሐው​ልት ቀጠ​ቀጡ፤ የበ​ዓ​ል​ንም ቤት አፈ​ረሱ፤ እስከ ዛሬም ድረስ የው​ዳቂ መጣያ አደ​ረ​ጉት።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ለዳ​ዊ​ትና ለልጁ ለሰ​ሎ​ሞን፥ “በዚህ ቤት ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ነገድ ሁሉ በመ​ረ​ጥ​ኋት በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ስሜን ለዘ​ለ​ዓ​ለም አኖ​ራ​ለሁ፤


የይ​ሁ​ዳም ነገ​ሥ​ታት ያሠ​ሩ​ትን በአ​ካዝ ቤት ሰገ​ነት ላይ የነ​በ​ሩ​ትን መሠ​ዊ​ያ​ዎች፥ ምና​ሴም ያሠ​ራ​ውን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት በሁ​ለቱ ወለ​ሎች ላይ የነ​በ​ሩ​ትን መሠ​ዊ​ያ​ዎች ንጉሡ አስ​ፈ​ረ​ሳ​ቸው፤ ከዚ​ያም አወ​ረ​ዳ​ቸው፤ አደ​ቀ​ቃ​ቸ​ውም፥ ትቢ​ያ​ቸ​ው​ንም በቄ​ድ​ሮን ፈፋ ጣለ።


ደግ​ሞም በቤ​ቴል ኮረ​ብታ የነ​በ​ረ​ውን መሠ​ዊያ፥ እስ​ራ​ኤ​ል​ንም ያሳተ የና​ባጥ ልጅ ኢዮ​ር​ብ​ዓም ያሠ​ራ​ውን የኮ​ረ​ብ​ታ​ውን መስ​ገጃ፥ ይህ​ንም መሠ​ዊ​ያና መስ​ገጃ አፈ​ረሰ፤ ድን​ጋ​ዮ​ቹ​ንም ሰባ​በረ፤ አድ​ቅ​ቆም ትቢያ አደ​ረ​ገው፤ የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ዱ​ንም አቃ​ጠ​ለው።


ንጉ​ሡም አሳ እና​ቱን መዓ​ካን ለአ​ስ​ጣ​ር​ቴስ ስለ ሰገ​ደች ከእ​ቴ​ጌ​ነቷ አወ​ረ​ዳት፤ አሳም ምስ​ሉን ቈርጦ ቀጠ​ቀ​ጠው፤ በቄ​ድ​ሮ​ንም ወንዝ አጠ​ገብ አቃ​ጠ​ለው።


አባ​ቱም ሕዝ​ቅ​ያስ ያፈ​ረ​ሳ​ቸ​ውን የኮ​ረ​ብታ መስ​ገ​ጃ​ዎች መልሶ ሠራ፤ ለበ​ዓ​ሊ​ምም መሠ​ዊያ ሠራ፤ የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ዶ​ች​ንም ተከለ፤ ለሰ​ማ​ይም ሠራ​ዊት ሁሉ ሰገደ፤ አመ​ለ​ካ​ቸ​ውም።


የበ​ዓ​ሊ​ም​ንም መሠ​ዊ​ያ​ዎች በፊቱ አፈ​ረሰ፤ በላ​ዩም የነ​በ​ሩ​ትን ኮረ​ብ​ታ​ዎ​ችን ዐፀ​ዶ​ቹ​ንም ቈረጠ፤ የተ​ቀ​ረ​ጹ​ት​ንና ቀል​ጠው የተ​ሠ​ሩ​ት​ንም ምስ​ሎች ሰባ​በረ፤ አደ​ቀ​ቃ​ቸ​ውም፤ ይሠ​ዉ​ላ​ቸው በነ​በ​ሩት ሰዎች መቃ​ብ​ርም ላይ በተ​ና​ቸው።


የሠ​ሩ​ት​ንም ጥጃ ወስዶ በእ​ሳት አቀ​ለ​ጠው፤ ፈጨው፤ አደ​ቀ​ቀ​ውም፤ በው​ኃም ላይ በተ​ነው፤ ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች አጠ​ጣ​ቸው።


ልጆ​ቻ​ቸ​ውም ከለ​መ​ለሙ ዛፎች በታ​ችና በረ​ዘ​ሙት ኮረ​ብ​ቶች ላይ ያሉ​ትን መሠ​ዊ​ያ​ቸ​ው​ንና የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ዳ​ቸ​ውን ያስ​ባሉ።


ስለ​ዚህ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ስለ ይሁዳ ንጉሥ ስለ ኢዮ​ስ​ያስ ልጅ ስለ ኢዮ​አ​ቄም እን​ዲህ ይላል፥ “ወን​ድሜ ሆይ፥ ወዮ! ጌታዬ ሆይ፥ ወዮ! እያለ የሚ​ያ​ለ​ቅ​ስ​ለት ለሌ​ለው ለዚያ ሰው ወዮ​ለት!


የአ​ስ​ሬ​ሞ​ትም ሸለቆ ሁሉ እስከ ቄድ​ሮን ወንዝ ድረስ በም​ሥ​ራቅ በኩል እስ​ካ​ለው እስከ ፈረስ በር ማዕ​ዘን ድረስ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​ቀ​ደሰ ይሆ​ናል፤ ከእ​ን​ግ​ዲ​ህም ወዲህ ለዘ​ለ​ዓ​ለም አይ​ነ​ቀ​ልም፤ አይ​ፈ​ር​ስ​ምም።


ጌታ​ችን ኢየ​ሱ​ስም ይህን ተና​ግሮ አት​ክ​ልት ወደ አለ​በት ስፍራ ወደ ቄድ​ሮስ ወንዝ ማዶ ከደቀ መዛ​ሙ​ርቱ ጋር ወጣ፤ ከደቀ መዛ​ሙ​ር​ቱም ጋር ወደ​ዚያ ገባ።


የአ​ም​ላ​ኮ​ቻ​ቸ​ውን ምስል በእ​ሳት ታቃ​ጥ​ላ​ለህ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም የተ​ሠ​ራ​ባ​ቸ​ውን ብር​ንና ወር​ቅን፥ አት​መኝ፤ በአ​ም​ላ​ክ​ህም በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ ርኩስ ነውና እን​ዳ​ት​በ​ድ​ል​በት ከእ​ርሱ ምንም አት​ው​ሰድ።


ስለ አደ​ረ​ጋ​ች​ሁ​ትም ኀጢ​አት የጥ​ጃ​ውን ምስል ወሰ​ድሁ፤ በእ​ሳ​ትም አቃ​ጠ​ል​ሁት፤ አደ​ቀ​ቅ​ሁ​ትም፤ እንደ ትቢ​ያም እስ​ኪ​ሆን ድረስ ፈጨ​ሁት፤ እንደ ትቢ​ያም ሆነ፤ ትቢ​ያ​ው​ንም ከተ​ራ​ራው በሚ​ወ​ርድ ወንዝ ጨመ​ር​ሁት።


የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ክፉ አደ​ረጉ፤ አም​ላ​ካ​ቸ​ው​ንም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ረስ​ተው በዓ​ሊ​ም​ንና አስ​ታ​ሮ​ትን አመ​ለኩ።


跟着我们:

广告


广告