Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




2 ዜና መዋዕል 7:20 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

20 እኔም ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ችሁ ከሰ​ጠ​ኋ​ቸው ምድር እነ​ቅ​ላ​ች​ኋ​ለሁ፤ ለስ​ሜም የቀ​ደ​ስ​ሁ​ትን ይህን ቤት ከፊቴ እጥ​ለ​ዋ​ለሁ፤ በአ​ሕ​ዛ​ብም ሁሉ መካ​ከል ምሳ​ሌና ተረት አደ​ር​ገ​ዋ​ለሁ።

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

20 በዚያ ጊዜ እስራኤልን ከሰጠኋቸው ምድሬ እነቅላቸዋለሁ፤ ለስሜ የቀደስሁትን ይህን ቤተ መቅደስ እተወዋለሁ፤ በሕዝቦችም ሁሉ ዘንድ መተረቻና መዘባበቻ አደርገዋለሁ።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

20 ለአባቶቻችሁ ከሰጠኋቸው ምድር እነቅላችኋለሁ፤ ለስሜም የቀደስሁትን ይህን ቤት ከፊቴ አርቄ እጥለዋለሁ፥ በአሕዛብም ሁሉ መካከል ምሳሌና መሳለቂያ አደርገዋለሁ።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

20 እኔ ከሰጠኋችሁ ከምድሬ ተነቅላችሁ እንድትባረሩ አደርጋለሁ፤ እኔ ለስሜ የቀደስኩትን ይህን ቤተ መቅደስ እተወዋለሁ፤ በሁሉ ስፍራ የሚኖሩ ሕዝቦችም በንቀት መሳለቂያና መዘባበቻ ያደርጉታል።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

20 ለአባቶቻችሁ ከሰጠኋቸው ምድር እነቅላችኋለሁ፤ ለስሜም የቀደስሁትን ይህን ቤት ከፊቴ እጥለዋለሁ፤ በአሕዛብም ሁሉ መካከል ምሳሌና ተረት አደርገዋለሁ።

参见章节 复制




2 ዜና መዋዕል 7:20
21 交叉引用  

በዚያ ጊዜም ሸም​በቆ በውኃ ውስጥ እን​ደ​ሚ​ን​ቀ​ሳ​ቀስ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲሁ እስ​ራ​ኤ​ልን ይመ​ታል፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ያስ​ቈጡ ዘንድ የማ​ም​ለ​ኪያ አፀድ ተክ​ለ​ዋ​ልና ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸው ከሰ​ጣ​ቸው ከዚች ከመ​ል​ካ​ሚቱ ምድር እስ​ራ​ኤ​ልን ይነ​ቅ​ላል፤ በወ​ን​ዙም ማዶ ይበ​ት​ና​ቸ​ዋል።


እስ​ራ​ኤ​ልን ከሰ​ጠ​ኋ​ቸው ምድር አጠ​ፋ​ቸ​ዋ​ለሁ፤ ለስ​ሜም የቀ​ደ​ስ​ሁ​ትን ይህን ቤት ከፊቴ እጥ​ለ​ዋ​ለሁ፤ እስ​ራ​ኤ​ልም በአ​ሕ​ዛብ ሁሉ መካ​ከል ለጥ​ፋ​ትና ለተ​ረት ይሆ​ናሉ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በእ​ስ​ራ​ኤል ዘር ሁሉ ተቈጣ፤ አስ​ጨ​ነ​ቃ​ቸ​ውም፤ ከፊ​ቱም እስ​ኪ​ጥ​ላ​ቸው ድረስ በበ​ዝ​ባ​ዦች እጅ አሳ​ልፎ ሰጣ​ቸው።


የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ቤተ መቅ​ደስ አቃ​ጠለ፤ የኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንም ቅጥር አፈ​ረሰ፤ አዳ​ራ​ሾ​ች​ዋ​ንም በእ​ሳት አቃ​ጠለ፤ መል​ካ​ሙ​ንም ዕቃ​ዋን ሁሉ አጠፋ።


በኋ​ላዋ ደና​ግ​ሉን ለን​ጉሡ ይወ​ስ​ዳሉ፥ ባል​ን​ጀ​ሮ​ች​ዋ​ንም ወደ አንተ ያቀ​ር​ባሉ፤


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የግ​ብ​ዞ​ችን አጥ​ን​ቶች በት​ኖ​አ​ልና በዚያ የሚ​ያ​ስ​ፈራ ሳይ​ኖር እጅግ ፈሩ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አዋ​ር​ዶ​አ​ቸ​ዋ​ልና አፈሩ።


ባይ​መ​ለሱ ግን ያን ሕዝብ እነ​ቅ​ለ​ዋ​ለሁ፤ አስ​ወ​ግ​ደ​ዋ​ለሁ፤ አጠ​ፋ​ው​ማ​ለሁ፤” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


ስለ​ዚህ ከዚች ምድር እና​ን​ተና አባ​ቶ​ቻ​ችሁ ወደ አላ​ወ​ቃ​ች​ኋት ምድር እጥ​ላ​ች​ኋ​ለሁ፤ በዚ​ያም ምሕ​ረ​ትን ለማ​ያ​ደ​ር​ጉ​ላ​ችሁ ሌሎች አማ​ል​ክት ቀንና ሌሊት ታገ​ለ​ግ​ላ​ላ​ችሁ።”


አጠ​ፋ​ቸ​ውና እደ​መ​ስ​ሳ​ቸው ዘንድ በሕ​ዝብ ላይና በመ​ን​ግ​ሥት ላይ ቍርጥ ነገ​ርን ተና​ገ​ርሁ፤


ብዙ አሕ​ዛ​ብም በዚች ከተማ ላይ ያል​ፋሉ፤ ሁሉም ባል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸ​ውን፦ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በዚች ታላቅ ከተማ ለምን እን​ዲህ አደ​ረገ? ይላሉ።


በማ​ሳ​ድ​ዳ​ቸ​ውም ስፍራ ሁሉ ለስ​ድ​ብና ለም​ሳሌ፥ ለጥ​ላ​ቻና ለር​ግ​ማን ይሆኑ ዘንድ በም​ድር መን​ግ​ሥ​ታት ሁሉ እን​ዲ​በ​ተኑ አደ​ር​ጋ​ለሁ።


እን​ዲ​ህም ይሆ​ናል፤ አፈ​ር​ሳ​ቸ​ውና ክፉ አደ​ር​ግ​ባ​ቸው ዘንድ እንደ ተጋ​ሁ​ባ​ቸው፥ እን​ዲሁ እሠ​ራ​ቸ​ውና እተ​ክ​ላ​ቸው ዘንድ እተ​ጋ​ለሁ፥” ይላል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር።


ሰው​ነ​ታ​ች​ሁ​ንም ታጠፉ ዘንድ፥ በም​ድ​ርም አሕ​ዛብ ሁሉ መካ​ከል መረ​ገ​ሚ​ያና መሰ​ደ​ቢያ ትሆኑ ዘንድ፥ ለመ​ቀ​መጥ በገ​ባ​ች​ሁ​ባት በግ​ብፅ ምድር ለሌ​ሎች አማ​ል​ክት በማ​ጠ​ና​ችሁ በእ​ጃ​ችሁ ሥራ ለምን ታስ​ቈ​ጡ​ኛ​ላ​ችሁ?


እን​ዲህ በለው፦ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ዲህ ይላል፦ እነሆ የሠ​ራ​ሁ​ትን አፈ​ር​ሳ​ለሁ፥ የተ​ከ​ል​ሁ​ት​ንም እነ​ቅ​ላ​ለሁ፤ ይኸ​ውም በም​ድር ሁሉ ነው።


ከአ​ሕ​ዛብ ዘንድ ከሁሉ የሚ​ከ​ፉ​ትን አመ​ጣ​ለሁ፤ ቤታ​ቸ​ው​ንም ይወ​ር​ሳሉ፥ የኀ​ያ​ላ​ን​ንም ትዕ​ቢት አጠ​ፋ​ለሁ፤ መቅ​ደ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም ይረ​ክ​ሳሉ።


እር​ሱን ትታ​ች​ሁ​ታ​ልና ዳግ​መ​ኛም በም​ድረ በዳ ትታ​ች​ሁ​ታል፤ በዚ​ችም ማኅ​በር ሁሉ ላይ ትበ​ድ​ላ​ላ​ችሁ።”


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ወደ እነ​ርሱ በሚ​ወ​ስ​ድህ አሕ​ዛብ መካ​ከል ሁሉ የደ​ነ​ገ​ጥህ፥ ለም​ሳ​ሌና ለተ​ረ​ትም ትሆ​ና​ለህ።


ዛሬም እን​ዳሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በቍ​ጣና በመ​ቅ​ሠ​ፍት፥ በታ​ላ​ቅም መዓት ከም​ድ​ራ​ቸው ነቀ​ላ​ቸው፤ ወደ ሌላም ምድር ጣላ​ቸው።


እነዚህ ከእናንተ ጋር ሲጋበዙ በፍቅር ግብዣችሁ እንደ እድፍ ናቸው፤ እንደ እረኞች ያለ ፍርሃት ራሳቸውን ይጠብቃሉ፤ በነፋስ የተወሰዱ ውሃ የሌለባቸው ደመናዎች፥ ፍሬ የማያፈሩ ሁለት ጊዜ የሞቱ ከነሥራቸው የተነቀሉ በበጋ የደረቁ ዛፎች፥


跟着我们:

广告


广告