Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




2 ዜና መዋዕል 35:19 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

19 ይህም ፋሲካ ኢዮ​ስ​ያስ በነ​ገሠ በዐ​ሥራ ስም​ን​ተ​ኛው ዓመት ተደ​ረገ። 19 ‘ሀ’ ንጉሡ ኢዮ​ስ​ያስ ካህኑ ኬል​ቅ​ያስ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ባገ​ኘው መጽ​ሐፍ የተ​ጻ​ፉ​ትን ቃላት ሁሉ ለመ​ጠ​በቅ አስ​ማ​ተ​ኞ​ች​ንና ጠን​ቋ​ዮ​ችን፥ ሟር​ተ​ኞ​ች​ንና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ምድ​ርና በይ​ሁዳ የሚ​ገ​ኙ​ትን ምስ​ሎ​ችና ቃሪ​ያ​ሲም የተ​ባሉ ጣዖ​ታ​ትን በእ​ሳት አቃ​ጠለ። 19 ‘ለ’ እንደ ሙሴ ሕግ ሁሉ በፍ​ጹም ልቡ፥ በፍ​ጹም ነፍሱ፥ በፍ​ጹም ኀይሉ ከእ​ርሱ በፊት ከነ​በ​ሩት ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የተ​መ​ለሰ የሚ​መ​ስ​ለው ሰው አል​ነ​በ​ረም። ከእ​ር​ሱም በኋላ የሚ​መ​ስ​ለው አል​ተ​ነ​ሣም። 19 ‘ሐ’ ነገር ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ንጉሥ ምናሴ በይ​ሁዳ ላይ በአ​ደ​ረ​ገ​ውና በአ​ነ​ሣ​ሣው ጥፋት ሁሉ ከአ​ስ​ከ​ተ​ለው ታላቅ ቍጣ አል​ተ​መ​ለ​ሰም። 19 ‘መ’ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም አለ፥ “እስ​ራ​ኤ​ልን እን​ዳ​ራ​ቅሁ ይሁ​ዳን ከፊቴ አር​ቃ​ለሁ። የመ​ረ​ጥ​ኋ​ት​ንም ከተማ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ም​ንና ስሜ በዚያ ይጠ​ራ​በ​ታል ያል​ሁ​ትን ቤት እጥ​ላ​ለሁ።”

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

19 ይህ ፋሲካ የተከበረው በኢዮስያስ ዘመነ መንግሥት በዐሥራ ስምንተኛው ዓመት ነበር።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

19 ይህም ፋሲካ ኢዮስያስ በነገሠ በዓሥራ ስምንተኛው ዓመት ተከበረ።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

19 ይህም በዓል የተከበረው፥ ኢዮስያስ በነገሠ በዐሥራ ስምንተኛው ዓመት ነበር።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

19 ይህም ፋሲካ ኢዮስያስ በነገሠ በአሥራ ስምንተኛው ዓመት ተደረገ።

参见章节 复制




2 ዜና መዋዕል 35:19
3 交叉引用  

እን​ደ​ዚ​ህም ያለ ፋሲካ በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ይፈ​ርዱ ከነ​በሩ ከመ​ሳ​ፍ​ንት ዘመን ጀምሮ በእ​ስ​ራ​ኤ​ልና በይ​ሁዳ ነገ​ሥ​ታት ዘመን ሁሉ አል​ተ​ደ​ረ​ገም።


ከነ​ቢ​ዩም ከሳ​ሙ​ኤል ዘመን ጀምሮ እን​ደ​ዚህ ያለ ፋሲካ በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ ከቶ አል​ተ​ደ​ረ​ገም፤ ከእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ነገ​ሥ​ታት ሁሉ ኢዮ​ስ​ያ​ስና ካህ​ናቱ፥ ሌዋ​ው​ያ​ኑም፥ በዚ​ያም የተ​ገኙ የይ​ሁ​ዳና የእ​ስ​ራ​ኤል ሰዎች ሁሉ፥ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም የሚ​ኖ​ሩት እን​ዳ​ደ​ረ​ጉት ያለ ፋሲካ ያደ​ረገ የለም።


ከዚ​ህም ሁሉ በኋላ፥ ኢዮ​ስ​ያ​ስም ቤተ መቅ​ደ​ሱን ካሰ​ናዳ በኋላ፥ የግ​ብጽ ንጉሥ ፈር​ዖን ኒካዑ በኤ​ፍ​ራ​ጥስ ወንዝ አጠ​ገብ የአ​ሦ​ርን ንጉሥ ይዋጋ ዘንድ ወጣ፤ ኢዮ​ስ​ያ​ስም ሊጋ​ጠ​መው ወጣ።


跟着我们:

广告


广告