Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




2 ዜና መዋዕል 15:8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

8 አሳም ይህን ቃልና የነ​ቢ​ዩን የአ​ዳ​ድን ልጅ የአ​ዛ​ር​ያ​ስን ትን​ቢት በሰማ ጊዜ ጸና፤ ከይ​ሁ​ዳና ከብ​ን​ያ​ምም ሀገር ሁሉ በተ​ራ​ራ​ማው በኤ​ፍ​ሬም ሀገር ከያ​ዛ​ቸው ከተ​ሞች ርኵ​ሰ​ትን ሁሉ አስ​ወ​ገደ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ቤት ፊት የነ​በ​ረ​ውን የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን መሠ​ዊያ አደሰ።

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

8 አሳ ይህን ቃልና የነቢዩን የዖዴድን ልጅ የዓዛርያስን ትንቢት በሰማ ጊዜ በረታ። ከመላው ይሁዳና ከብንያም ምድር፣ በኤፍሬምም ኰረብቶች ላይ ከያዛቸው ከተሞች አስጸያፊዎቹን ጣዖታት አስወገደ። ከእግዚአብሔር መቅደስ ሰበሰብ ፊት ለፊት የነበረውንም የእግዚአብሔር መሠዊያ ዐደሰ።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

8 አሳም እነዚህን ቃላትና የነቢዩን የዖዴድን ትንቢት በሰማ ጊዜ ልቡ ጸና፥ ከይሁዳና ከቢንያምም አገር ሁሉ በተራራማውም በኤፍሬም አገር ከያዛቸው ከተሞች ጸያፉን ነገር አስወገደ፤ በጌታም ቤት ፊት የነበረውን የጌታን መሠዊያ አደሰ።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

8 አሳ የዖዴድ ልጅ ዐዛርያስ የተናገረውን የትንቢት ቃል በሰማ ጊዜ ተበረታታ፤ በይሁዳና በብንያም ምድር እንዲሁም እርሱ ማርኮ በያዛቸው ኰረብታማ በሆነው በኤፍሬም ግዛት በሚገኙት ከተሞች ያሉትን አጸያፊ ጣዖቶች ሁሉ አስወገደ፤ በቤተ መቅደሱ ቅጽር ግቢ ውስጥ ቆሞ የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠዊያ አደሰ።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

8 አሳም ይህን ቃልና የነቢዩን የዖዴድን ትንቢት በሰማ ጊዜ ልቡ ጸና፤ ከይሁዳና ከቢንያምም አገር ሁሉ በተራራማውም በኤፍሬም አገር ከያዛቸው ከተሞች ጸያፉን ነገር አስወገደ፤ በእግዚአብሔርም ቤት ፊት የነበረውን የእግዚአብሔርን መሠዊያ አደሰ።

参见章节 复制




2 ዜና መዋዕል 15:8
24 交叉引用  

ሰሎ​ሞ​ንም የሲ​ዶ​ና​ው​ያ​ንን አም​ላክ አስ​ጠ​ራ​ጢ​ስን የአ​ሞ​ና​ው​ያ​ን​ንም ርኵ​ሰት ኮሞ​ስን ተከ​ተለ።


ያን​ጊ​ዜም ሰሎ​ሞን ለሞ​አብ ርኵ​ሰት ለኮ​ሞስ፥ ለአ​ሞን ልጆች ርኵ​ሰት ለሞ​ሎክ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም አን​ጻር በአ​ለው ተራራ ላይ መስ​ገ​ጃን ሠራ።


በእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ በኢ​ዮ​ር​ብ​ዓም በሃያ አራ​ተ​ኛው ዓመት አሳ በይ​ሁዳ ላይ ነገሠ።


በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት የነ​በ​ረ​ውን የና​ሱን መሠ​ዊያ ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ፊት ከመ​ሠ​ዊ​ያ​ውና ከእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት መካ​ከል ፈቀቅ አድ​ርጎ በመ​ሠ​ዊ​ያው አጠ​ገብ በሰ​ሜን በኩል አኖ​ረው።


እና​ን​ተም፦ በአ​ም​ላ​ካ​ችን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እን​ታ​መ​ና​ለን ብት​ሉኝ፥ ሕዝ​ቅ​ያስ ይሁ​ዳ​ንና ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምን፦ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ባለው በዚህ መሠ​ዊያ ፊት ስገዱ ብሎ የኮ​ረ​ብታ መስ​ገ​ጃ​ዎ​ቹ​ንና መሠ​ዊ​ያ​ዎ​ቹን ያስ​ፈ​ረሰ ይህ አይ​ደ​ለ​ምን?


በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ፊት ለፊት በር​ኵ​ስት ተራራ ቀኝ የነ​በ​ሩ​ትን፥ የእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ ሰሎ​ሞን ለሲ​ዶ​ና​ው​ያን ርኵ​ስት ለአ​ስ​ታ​ሮት፥ ለሞ​ዓ​ብም ርኵ​ሰት ለካ​ሞሽ፥ ለአ​ሞ​ንም ልጆች ርኵ​ሰት ለሞ​ሎክ ያሠ​ራ​ቸ​ውን መስ​ገ​ጃ​ዎች ንጉሡ ርኩስ አደ​ረገ።


አብ​ያም ኢዮ​ር​ብ​ዓ​ምን ተከ​ትሎ አሳ​ደ​ደው፤ ከእ​ር​ሱም ከተ​ሞ​ቹን ቤቴ​ል​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋን፥ ይሳ​ና​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋን፥ ዔፍ​ሮ​ን​ንና መን​ደ​ሮ​ች​ዋን ወሰደ።


በተ​መ​ሸ​ጉ​ትም በይ​ሁዳ ከተ​ሞች ሁሉ ሠራ​ዊ​ቱን አኖረ፤ በይ​ሁ​ዳም ሀገር፥ አባ​ቱም አሳ በወ​ሰ​ዳ​ቸው በኤ​ፍ​ሬም ከተ​ሞች መሳ​ፍ​ን​ቱን አስ​ቀ​መጠ።


እነ​ሆም፥ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሚ​ሆ​ነው ነገር ሁሉ የካ​ህ​ናቱ አለቃ አማ​ርያ፥ በን​ጉ​ሡም ነገር ሁሉ የይ​ሁዳ ቤት አለቃ የይ​ስ​ማ​ኤል ልጅ ዝባ​ድ​ያስ በላ​ያ​ችሁ ተሾ​መ​ዋል፤ ጸሐ​ፍ​ቱና ሌዋ​ው​ያኑ ደግሞ በፊ​ታ​ችሁ አሉ፤ በር​ት​ታ​ች​ሁም አድ​ርጉ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መል​ካም ከሚ​ያ​ደ​ርግ ጋር ይሁን።


ኢዮ​ሣ​ፍ​ጥም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ተቀ​መጠ፤ ደግ​ሞም ከቤ​ር​ሳ​ቤህ ጀምሮ እስከ ተራ​ራ​ማው እስከ ኤፍ​ሬም ሀገር ድረስ ወደ ሕዝቡ ወጥቶ ወደ አባ​ቶ​ቻ​ቸው አም​ላክ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መለ​ሳ​ቸው።


ወደ ውስ​ጡም ወደ ንጉሡ ወደ ሕዝ​ቅ​ያስ ገብ​ተው፥ “የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ቤት ሁሉ፥ ለሚ​ቃ​ጠል መሥ​ዋ​ዕት የሚ​ሆ​ነ​ውን መሠ​ዊ​ያና ዕቃ​ው​ንም ሁሉ፥ የኅ​ብ​ስተ ገጹ​ንም ገበ​ታና ዕቃ​ውን ሁሉ አን​ጽ​ተ​ናል፤


ርዝ​መ​ቱም ሃያ ክንድ፥ ወር​ዱም ሃያ ክንድ፥ ቁመ​ቱም ዐሥር ክንድ የነ​በ​ረ​ውን የና​ሱን መሠ​ዊያ ሠራ።


በዚያ ጊዜም ሰሎ​ሞን በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ፊት በሠ​ራው በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መሠ​ዊያ ላይ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕት አቀ​ረበ።


እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያበ​ቀ​ለ​ውን፥ በዝ​ና​ምም ያሳ​ደ​ገ​ውን ዛፍ ከዱር ይቈ​ር​ጣል።


በመ​ቃ​ብ​ርም መካ​ከል የሚ​ተኙ፥ በዋሻ ውስጥ የሚ​ያ​ልሙ፥ የእ​ሪያ ሥጋም የሚ​በሉ ናቸው። የመ​ሥ​ዋ​ዕ​ታ​ቸ​ውን ደምና ዕቃ​ቸ​ው​ንም ሁሉ ያረ​ክ​ሳሉ።


ምድ​ሬ​ንም በተ​ጠሉ በጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸው ሬሳ​ዎች አር​ክ​ሰ​ዋ​ልና፥ ርስ​ቴ​ንም አስ​ጸ​ያፊ በሆኑ ነገ​ሮች ሞል​ተ​ዋ​ልና አስ​ቀ​ድሜ የበ​ደ​ላ​ቸ​ው​ንና የኀ​ጢ​አ​ታ​ቸ​ውን ዕዳ ሁለት እጥፍ እከ​ፍ​ላ​ቸ​ዋ​ለሁ።”


እኔም ገባ​ሁና፥ እነሆ በግ​ንቡ ዙሪያ ላይ የተ​ን​ቀ​ሳ​ቃ​ሾች አዕ​ዋ​ፍና እን​ስ​ሳ​ትን ምሳሌ ከን​ቱና ርኩስ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ቤት ጣዖ​ታት ሁሉ ተሥ​ለው አየሁ።


ስለ​ዚህ ከእ​ና​ንተ በፊት የነ​በሩ ሰዎች የሠ​ሩ​ትን ጸያፍ የሆ​ነ​ውን ወግ ሁሉ እን​ዳ​ት​ሠሩ፥ በእ​ር​ሱም እን​ዳ​ት​ረ​ክሱ ሥር​ዐ​ቴን ጠብቁ፤ እኔ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አም​ላ​ካ​ችሁ ነኝና።”


አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት፤ ሌላም አምስት አተረፈ፤


በዚ​ያም ያሉት ወን​ድ​ሞች ስለ እኛ በሰሙ ጊዜ፤ አፍ​ዩስ ፋሩስ እስ​ከ​ሚ​ባ​ለው ገበ​ያና እስከ ሦስ​ተ​ኛው ማረ​ፊያ ድረስ ወጥ​ተው ተቀ​በ​ሉን፤ ጳው​ሎ​ስም ባያ​ቸው ጊዜ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አመ​ሰ​ገነ፤ ልቡም ተጽ​ናና።


“በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዘንድ የተ​ጠላ የሠ​ራ​ተኛ እጅ ሥራን፥ የተ​ቀ​ረፀ ወይም ቀልጦ የተ​ሠራ ምስ​ልን የሚ​ያ​ደ​ርግ፥ በስ​ው​ርም የሚ​ያ​ቆ​መው ሰው ርጉም ይሁን፤ ሕዝ​ቡም ሁሉ መል​ሰው አሜን ይላሉ።


የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለ ልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣዖት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ይበቃልና።


ሌሎ​ች​ንም አማ​ል​ክት ከመ​ካ​ከ​ላ​ቸው አስ​ወ​ገዱ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ብቻ አመ​ለኩ፤ ደስም አሰ​ኙት፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ከሥ​ቃይ የተ​ነሣ አእ​ም​ሮ​አ​ቸ​ውን አጥ​ተው ነበር።


跟着我们:

广告


广告