Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -




1 ነገሥት 16:29 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

29 በይ​ሁ​ዳም ንጉሥ በኢ​ዮ​ሳ​ፍጥ በሁ​ለ​ተ​ኛው ዓመት የዘ​ን​በሪ ልጅ አክ​ዓብ በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ በሰ​ማ​ርያ ሃያ ሁለት ዓመት ነገሠ።

参见章节 复制

አዲሱ መደበኛ ትርጒም

29 የይሁዳ ንጉሥ አሳ በነገሠ በሠላሳ ስምንተኛው ዓመት፣ የዖምሪ ልጅ አክዓብ በእስራኤል ላይ ነገሠ፣ በሰማርያም ሆኖ እስራኤልን ሃያ ሁለት ዓመት ገዛ።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)

29 አሳ በይሁዳ በነገሠ በሠላሳ ስምንተኛው ዓመት የዖምሪ ልጅ አክዓብ የእስራኤል ንጉሥ ሆነ፤ እርሱም መኖሪያውን በሰማርያ አድርጎ ኻያ ሁለት ዓመት ገዛ።

参见章节 复制

አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም

29 አሳ በይሁዳ በነገሠ በሠላሳ ስምንተኛው ዓመት የዖምሪ ልጅ አክዓብ የእስራኤል ንጉሥ ሆነ፤ እርሱም መኖሪያውን በሰማርያ አድርጎ ኻያ ሁለት ዓመት ገዛ።

参见章节 复制

መጽሐፍ ቅዱስ (የብሉይና የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት)

29 በይሁዳም ንጉሥ በአሳ በሠላሳ ስምንተኛው ዓመት የዖምሪ ልጅ አክዓብ በእስራኤል ላይ ነገሠ፤ የዖምሪም ልጅ አክዓብ በእስራኤል ላይ በሰማሪያ ኻያ ሁለት ዓመት ነገሠ።

参见章节 复制




1 ነገሥት 16:29
11 交叉引用  

በዚ​ያም ጊዜ የእ​ስ​ራ​ኤል ሕዝብ በሁ​ለት ተከ​ፈለ፤ የሕ​ዝ​ቡም እኩ​ሌታ የጎ​ና​ትን ልጅ ታም​ኒን ያነ​ግ​ሡት ዘንድ ተከ​ተ​ሉት፤ እኩ​ሌ​ቶ​ችም ዘን​በ​ሪን ተከ​ተሉ።


በይ​ሁዳ ንጉሥ በአሳ በሠ​ላሳ አን​ደ​ኛው ዓመተ መን​ግ​ሥት ዘን​በሪ በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ዐሥራ ሁለት ዓመት ነገሠ። በቴ​ር​ሳም ስድ​ስት ዓመት ነገሠ።


ዘን​በ​ሪም ከዚ​ያች ተራራ ባለ​ቤት ከሴ​ሜር በሁ​ለት መክ​ሊት ብር የሳ​ም​ሮ​ንን ተራራ ገዛ፤ በተ​ራ​ራ​ውም ላይ ከተማ ሠራ፤ የሠ​ራ​ት​ንም ከተማ በተ​ራ​ራው ባለ​ቤት በሳ​ምር ስም ሰማ​ርያ ብሎ ጠራት።


ዘን​በ​ሪም ከአ​ባ​ቶቹ ጋር አን​ቀ​ላፋ፥ በሰ​ማ​ር​ያም ቀበ​ሩት፤ ልጁም አክ​አብ በፋ​ን​ታው ነገሠ። 28 ‘ሀ’ ዘን​በ​ሪም ዐሥራ አንድ ዓመት ሲሆ​ነው የአሳ ልጅ ኢዮ​ሳ​ፍጥ ነገሠ። በነ​ገ​ሠም ጊዜ ሠላሳ አም​ስት ዓመት ሆኖት ነበረ፤ በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ሃያ አም​ስት ዓመት ነገሠ፤ እና​ቱም ጋዙባ የም​ት​ባል የሴ​ላህ ልጅ ነበ​ረች። 28 ‘ለ’ በአ​ባ​ቱም በአሳ መን​ገድ ሄደ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ጽድ​ቅን ያደ​ርግ ዘንድ ከእ​ር​ስዋ ፈቀቅ አላ​ለም። በተ​ራ​ሮች የነ​በ​ሩ​ት​ንም አማ​ል​ክት አላ​ስ​ወ​ገ​ደም፤ ሕዝ​ቡም በተ​ራ​ሮቹ ይሠ​ዉ​ላ​ቸ​ውና ያጥ​ኑ​ላ​ቸው ነበረ። 28 ‘ሐ’ ኢዮ​ሳ​ፍ​ጥም ከእ​ስ​ራ​ኤል ንጉሥ ጋር የሠ​ራው፥ የተ​ዋ​ጋ​ውና ያደ​ረ​ገው ኀይል ሁሉ እነሆ፥ በይ​ሁዳ ነገ​ሥ​ታት የታ​ሪክ መጽ​ሐፍ የተ​ጻፈ ነው። 28 ‘መ’ በአ​ባ​ቱም በአሳ ዘመን የነ​በ​ረ​ውን ርኵ​ሰት ሁሉ ከም​ድር አስ​ወ​ገደ። በኤ​ዶ​ምም ንጉሥ አል​ነ​በ​ረም። 28 ‘ሠ’ ንጉሥ ኢዮ​ሳ​ፍ​ጥም ወር​ቅና ብርን ሊያ​መ​ጡ​ለት ወደ አፌር ይልክ ዘንድ በተ​ር​ሴስ መር​ከብ አሠራ፤ በጋ​ስ​ዮንጋቤር የነ​በ​ረ​ችው መር​ከብ ተሰ​ብ​ራ​ለ​ችና አል​ሄ​ደ​ችም። 28 ‘ረ’ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ንጉሥ አካ​ዝ​ያስ ኢዮ​ሳ​ፍ​ጥን፥ “አገ​ል​ጋ​ዮ​ች​ህ​ንና አገ​ል​ጋ​ዮቼን በመ​ር​ከብ እን​ላክ” አለው። ኢዮ​ሳ​ፍ​ጥም እንቢ አለ። 28 ‘ሰ’ ኢዮ​ሳ​ፍ​ጥም እንደ አባ​ቶቹ አን​ቀ​ላፋ። በዳ​ዊ​ትም ከተማ ከአ​ባ​ቶቹ ጋር ተቀ​በረ። በእ​ር​ሱም ፋንታ ልጁ ኢዮ​ራም ነገሠ።


አክ​ዓ​ብም ከእ​ርሱ በፊት ከነ​በ​ሩት ሁሉ ይልቅ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት ክፉ አደ​ረገ።


አክ​ዓ​ብም የማ​ም​ለ​ኪያ ዐፀ​ድን አሠራ፤ አክ​ዓ​ብም ሰው​ነቱ እን​ድ​ት​ጠፋ ከእ​ርሱ በፊት ከነ​በ​ሩት ከእ​ስ​ራ​ኤል ነገ​ሥ​ታት ሁሉ ይልቅ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ያ​ስ​ቈ​ጣ​ውን ነገር አበዛ።


እር​ሱም፥ “ለሰ​ላም መጥ​ተው እንደ ሆነ በሕ​ይ​ወ​ታ​ቸው ያዙ​አ​ቸው፤ ለው​ጊያ መጥ​ተው እንደ ሆነ ግን ተዋ​ጓ​ቸው” አለ።


አሜ​ስ​ያስ ግን ከእ​ርሱ ጋር ወደ ሰልፍ እን​ዳ​ይ​ሄዱ ያሰ​ና​በ​ታ​ቸው ጭፍ​ሮ​ችም ከሰ​ማ​ርያ ጀም​ረው እስከ ቤት​ሮን ድረስ በይ​ሁዳ ከተ​ሞች ላይ አደጋ ጣሉ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም ሦስት ሺህ ገደሉ፤ ብዙም ምርኮ ማረኩ።


ጢማ​ቸ​ውን ላጭ​ተው፥ ልብ​ሳ​ቸ​ው​ንም ቀድ​ደው እያ​ለ​ቀሱ ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤት ያቀ​ርቡ ዘንድ የእ​ህል ቍር​ባ​ንና ዕጣን በእ​ጃ​ቸው የያዙ፥ ሰማ​ንያ ሰዎች ከሴ​ኬ​ምና ከሴሎ፥ ከሰ​ማ​ር​ያም መጡ።


ኤፍ​ሬም እንደ ተና​ገረ በእ​ስ​ራ​ኤል ሥር​ዐ​ቱን ወሰደ፤ ለበ​ዓ​ልም አደ​ረ​ገው፤ ሞተም።


አንተን ለጥፋት፥ በእርስዋም የሚኖሩትን ለማፍዋጫ እሰጥ ዘንድ የዘንበሪን ሥርዓትና የአክዓብን ቤት ሥራ ሁሉ ጠብቃችኋል፥ በምክራቸውም ሄዳችኋል፥ የሕዝቤንም ስድብ ትሸከማላችሁ።


跟着我们:

广告


广告