Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

ማሕልየ መሓልይ 6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)

1 አንቺ በሴ​ቶች ዘንድ የተ​ዋ​ብሽ ሆይ፥ ከአ​ንቺ ጋር እን​ፈ​ል​ገው ዘንድ ልጅ ወን​ድ​ምሽ ወዴት ሄደ? ልጅ ወን​ድ​ም​ሽስ ወዴት ፈቀቅ አለ?

2 ልጅ ወን​ድሜ በገ​ነቱ መን​ጋ​ውን ይጠ​ብቅ ዘንድ፥ አበ​ባ​ው​ንም ይሰ​በ​ስብ ዘንድ ወደ ሽቱ መደብ ወደ ገነቱ ወረደ።

3 እኔ የልጅ ወን​ድሜ ነኝ፥ ልጅ ወን​ድ​ሜም የእኔ ነው፤ በሱፍ አበባ መካ​ከል መን​ጋ​ውን ያሰ​ማ​ራል።

4 ወዳጄ ሆይ፥ እንደ ቴርሳ ውብ ነሽ፥ እንደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም ያማ​ርሽ ነሽ፤ ዓላማ ይዞ እንደ ተሰ​ለፈ ሠራ​ዊት ታስ​ፈ​ር​ያ​ለሽ።

5 ዐይ​ኖ​ች​ሽን ከፊቴ መልሺ፤ እነ​ርሱ አስ​ፈ​ር​ተ​ው​ኛ​ልና፤ ጠጕ​ርሽ ከገ​ለ​ዓድ እንደ ታየ እንደ ፍየል መንጋ ነው።

6 ጥር​ሶ​ችሽ ታጥ​በው እንደ ወጡ ሁሉም መንታ እንደ ወለዱ ከእ​ነ​ር​ሱም መካን እን​ደ​ሌ​ለ​ባ​ቸው መን​ጎች ናቸው። ከን​ፈ​ሮ​ችሽ እንደ ቀይ ሐር ናቸው፥ ቃልሽ ያማረ ነው።

7 ከዝ​ም​ታሽ በቀር ጕን​ጮ​ችሽ እንደ ተከ​ፈለ ሮማን ናቸው።

8 ስድሳ ንግ​ሥ​ታት፥ ሰማ​ን​ያም ቁባ​ቶች ቍጥር የሌ​ላ​ቸ​ውም ቈነ​ጃ​ጅት አሉ።

9 ርግቤ መደ​ም​ደ​ሚ​ያ​ዬም አን​ዲት ናት፤ ለእ​ናቷ አን​ዲት ናት፥ ለወ​ለ​ደ​ቻ​ትም የተ​መ​ረ​ጠች ናት። ቈነ​ጃ​ጅ​ትም አይ​ተው አሞ​ገ​ሱ​አት፥ ንግ​ሥ​ታ​ትና ቁባ​ቶ​ችም አመ​ሰ​ገ​ኑ​አት።

10 ይህች እንደ ማለዳ ብር​ሃን የም​ት​ጐ​በኝ፥ እንደ ጨረቃ የተ​ዋ​በች እንደ ፀሓ​ይም የጠ​ራች፥ ዓላማ ይዞ እንደ ተሰ​ለፈ ሠራ​ዊት የም​ታ​ስ​ፈራ ማን ናት?

11 ልጅ ወን​ድሜየወ​ን​ዙን ዳር ልም​ላሜ ያይ ዘንድ ወይኑ አብቦ ሮማ​ኑም አፍ​ርቶ እንደ ሆነ ይመ​ለ​ከት ዘንድ ወደ ገውዝ ገነት ወረደ።

12 በዚያ ጡቶ​ችን እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ፥ ሰው​ነ​ቴም አላ​ወ​ቀ​ችም፥ እንደ አሚ​ና​ዳብ ሰረ​ገላ አደ​ረ​ገኝ አለች። ብ. እና ግሪክ ሰባ. ሊ. “አይ ዘንድ ... ወረ​ድሁ” ይላል። ወይኑ አብቦ ሮማ​ኑም አፍ​ርቶ እንደ ሆነ ይመ​ለ​ከት ዘንድ ወደ ገውዝ ገነት ወረደ።

13 በዚያ ጡቶ​ችን እሰ​ጥ​ሃ​ለሁ፥ ሰው​ነ​ቴም አላ​ወ​ቀ​ችም፥ እንደ አሚ​ና​ዳብ ሰረ​ገላ አደ​ረ​ገኝ አለች።

跟着我们:



广告