Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 8 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የዮ​ዲት ትው​ል​ድና ተግ​ባር

1 በዚ​ያም ወራት የእ​ስ​ራ​ኤል ልጅ የሰ​ለ​ስ​ዳይ ልጅ፥ የሰ​ላ​ም​ያል ልጅ፥ የና​ት​ና​ኤል ልጅ፥ የኤ​ል​ያብ ልጅ፥ የኤ​ል​ያስ ልጅ፥ የሐ​ቂቆ ልጅ፥ የራ​ወ​ይል ልጅ፥ የጋ​ዴ​ዮን ልጅ፥ የአ​ና​ንዮ ልጅ፥ የሕ​ል​ቅያ ልጅ፥ የኦ​ዝ​ያል ልጅ፥ የዮ​ሴፍ ልጅ፥ የሆ​ክስ ልጅ፥ የሜ​ራሪ ልጅ ዮዲት ሰማች።

2 ባል​ዋም ከነ​ገ​ድ​ዋና ከሀ​ገ​ርዋ የሆነ ምናሴ ነበር፤ የገ​ብስ አዝ​መራ በደ​ረ​ሰ​በት ወራ​ትም ሞተ።

3 ነዶ ከሚ​ያ​ስሩ ሰዎች ጋራ በእ​ርሻ ውሏ​ልና ራሱን ምች መታው፤ ታምሞ ተኛ፤ በሀ​ገሩ በቤ​ጤ​ል​ዋም ሞተ፤ እንደ አባ​ቶ​ቹም በሀ​ገሩ በዶ​ታ​ይ​ምና በበ​ላ​ሞን ባለ ቦታ ቀበ​ሩት።

4 ዮዲ​ትም መበ​ለት ሆና ሦስት ዓመት ከአ​ራት ወር በቤ​ትዋ ተቀ​መ​ጠች።

5 በቤ​ት​ዋም ሰገ​ነት ላይ የብ​ሕ​ት​ውና ክፍል አዘ​ጋ​ጀች፤ በወ​ገ​ቧም ማቅ ታጠ​ቀች፤ የመ​በ​ለ​ት​ነት ልብ​ሷ​ንም ለበ​ሰች።

6 በመ​በ​ለ​ት​ነ​ትም በኖ​ረ​ች​በት ወራት ሁሉ ትጾም ነበር። በሰ​ን​በት ዋዜ​ማና በሰ​ን​በት፥ በመ​ባቻ ዋዜ​ማና በመ​ባቻ፥ በበ​ዓ​ላ​ትና በእ​ስ​ራ​ኤል የደ​ስታ ቀኖች ካል​ሆነ በቀር አት​በ​ላም ነበር።

7 መልከ መል​ካ​ምና እጅግ ደመ ግቡ ነበ​ረች፤ ባሏ ምና​ሴም ብሩ​ንና ወር​ቁን፥ ሴቶ​ችና ወን​ዶች አሽ​ከ​ሮ​ችን፥ ከብ​ቶ​ቹ​ንም፥ እር​ሻ​ው​ንም ትቶ​ላት ነበር፥ በእ​ነ​ር​ሱም ላይ ትኖር ነበር።

8 ፈጽማ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ትፈራ ነበ​ርና በእ​ርሷ ክፉ ቃልን የሚ​ና​ገር አል​ነ​በ​ረም።


ዮዲ​ትና የእ​ስ​ራ​ኤል ሽማ​ግ​ሌ​ዎች

9 ውኃው ስላ​ለቀ ሰው​ነ​ታ​ቸው ተጨ​ን​ቃ​ለ​ችና ሕዝቡ በአ​ለ​ቃ​ቸው ላይ የተ​ና​ገ​ሩ​ትን ክፉ ነገር ሰማች፤ ዮዲ​ትም ዖዝ​ያን ለሕ​ዝቡ የነ​ገ​ራ​ቸ​ውን ቃል ሁሉ፥ ከአ​ም​ስት ቀን በኋ​ላም ሀገ​ራ​ቸ​ውን ለአ​ሦር ሰዎች እን​ዲ​ሰጡ እንደ ማለ​ላ​ቸው ሰማች።

10 ገን​ዘ​ቧን ሁሉ የም​ት​ጠ​ብቅ ሞግ​ዚ​ት​ዋ​ንም ልካ ዖዝ​ያ​ንን፥ ከብ​ሪ​ኒ​ንና ከር​ሜ​ኒን፥ የከ​ተ​ማ​ዋ​ንም ሽማ​ግ​ሌ​ዎች ጠራ​ቻ​ቸው።

11 እነ​ር​ሱም ወደ እር​ስዋ መጡ፤ እር​ስ​ዋም “ዛሬ በሕ​ዝቡ ፊት የተ​ና​ገ​ራ​ች​ሁት በጎ ነገር አይ​ደ​ለ​ምና በቤ​ጤ​ልዋ የሚ​ኖሩ ሰዎች ሹሞች ሆይ! ስሙኝ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእ​ነ​ዚህ በአ​ም​ስቱ ቀኖች ባይ​ረ​ዳ​ችሁ ሀገ​ራ​ች​ሁን ለጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችሁ አሳ​ል​ፋ​ችሁ ትሰጡ ዘንድ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና በእ​ና​ንተ መካ​ከል የተ​ማ​ማ​ላ​ች​ሁ​ትን መሐላ በዚህ አጸ​ና​ችሁ።

12 አሁ​ንም በዚች ቀን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ት​ፈ​ታ​ተ​ኑት፥ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርና በሰው መካ​ከል የተ​ነ​ሣ​ችሁ እና​ንተ፥ ምን​ድን ናችሁ?

13 አሁ​ንም እርሱ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይመ​ረ​ም​ራል፤ እና​ንተ ግን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሁል​ጊዜ የሚ​ያ​ደ​ር​ገ​ውን አታ​ው​ቁም።

14 በሰው ልቡና ያለ ረቂቅ ምሥ​ጢ​ርን የማ​ታ​ውቁ፥ የል​ቡ​ና​ው​ንም አሳብ የማ​ታ​ስ​ተ​ውሉ ይህን ሁሉ ያደ​ረገ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እን​ዴት ትመ​ረ​ም​ራ​ላ​ችሁ? ልቡ​ና​ው​ንስ መር​ም​ራ​ችሁ ታውቁ ዘንድ እን​ዴት ትወ​ዳ​ላ​ችሁ? ምክ​ሩ​ንስ መር​ም​ራ​ችሁ ታገኙ ዘንድ እን​ዴት ትመ​ረ​ም​ራ​ላ​ችሁ? ወን​ድ​ሞች ሆይ፥ ለእ​ና​ንተ አግ​ባ​ባ​ችሁ አይ​ደ​ለም፤ አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም አታ​ሳ​ዝ​ኑት።

15 በእ​ነ​ዚህ በአ​ም​ስቱ ቀኖች ይረ​ዳን ዘንድ ባይ​ፈ​ቅድ በማ​ን​ኛ​ውም ቀን ቢሆን በፈ​ቀደ ጊዜ ሊያ​ድ​ነን፥ ወይም በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችን ፊት ሊያ​ጠ​ፋን ሥል​ጣን አለው።

16 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር እንደ ሰው የሚ​ጨ​ክን አይ​ደ​ለ​ምና እንደ ሰውም የሚ​ቀ​የም አይ​ደ​ለ​ምና፥ እና​ንተ አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን አት​ፈ​ታ​ተ​ኑት።

17 ነገር ግን ከእ​ርሱ የም​ት​ገኝ ድኅ​ነ​ትን ደጅ ጥኑ፤ ቃላ​ች​ን​ንም ሰምቶ ይረ​ዳን ዘንድ ይፈ​ቅድ እንደ ሆነ ለም​ኑት።

18 “በዘ​መ​ና​ችን ወይም ዛሬ በቀ​ድሞ ዘመን እንደ ተደ​ረገ ከእኛ መካ​ከል ወገ​ንም ቢሆን፥ ነገ​ድም ቢሆን፥ ከተ​ማም ቢሆን፥ መን​ደ​ርም ቢሆን በሰው እጅ ለተ​ሠሩ ጣዖ​ታት ለመ​ስ​ገድ የተ​ነሣ የለ​ምና።

19 ስለ​ዚ​ህም ነገር አባ​ቶ​ቻ​ችን ለመ​በ​ር​በ​ርና ለጦር ሆኑ፤ በጠ​ላ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ፊት ጽኑ አወ​ዳ​ደ​ቅን ወደቁ።

20 እኛ ግን ያለ​እ​ርሱ ሌላ አም​ላክ አና​ው​ቅም፤ ስለ​ዚህ እኛን ወይም ወገ​ኖ​ቻ​ች​ንን ቸል እን​ደ​ማ​ይ​ለን በእ​ርሱ እና​ም​ና​ለን።

21 እኛ በተ​ያ​ዝን ጊዜ ይሁዳ ሁሉ ይያ​ዛል፤ ንዋየ ቅድ​ሳ​ታ​ች​ንም ይዘ​ረ​ፋል፤ በመ​ቅ​ደ​ሱም መር​ከስ ከአ​ን​ደ​በ​ታ​ችን ይመ​ረ​መ​ራል።

22 የወ​ን​ድ​ሞ​ቻ​ችን መገ​ደል፥ የሀ​ገ​ራ​ች​ንም መዘ​ረፍ፥ የር​ስ​ታ​ች​ንም ምድረ በዳ መሆን በሚ​ገ​ዙን አሕ​ዛብ ዘንድ በእኛ ላይ ይመ​ለ​ሳል፤ ገን​ዘብ በሚ​ያ​ደ​ር​ጉን ፊትም በዚያ የተ​ሰ​ነ​ካ​ከ​ል​ንና መገ​ዳ​ደ​ሪያ እን​ሆ​ና​ለን።

23 መገ​ዛ​ታ​ች​ንም ያለ ምስ​ጋና ይሆ​ና​ልና፥ አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መዋ​ረ​ዳ​ች​ንን አላ​የ​ምና።

24 “አሁ​ንም ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችን ሆይ፥ ለባ​ል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ችን ንገ​ሩ​አ​ቸው፤ እኛን ያዳ​ም​ጣ​ሉና፥ ልቡ​ና​ቸ​ውም ወደ እኛ ተሰ​ቅ​ሏ​ልና፥ መሠ​ዊ​ያ​ዉና ቤተ መቅ​ደ​ሱም በእኛ ጸንቶ ይኖ​ራ​ልና።

25 አባ​ቶ​ቻ​ች​ንን እንደ ፈተ​ና​ቸው የሚ​ፈ​ት​ነን አም​ላ​ካ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን በዚህ ሁሉ እና​መ​ስ​ግ​ነው።

26 ለአ​ባ​ቶ​ቻ​ችን ያደ​ረ​ገ​ውን ሁሉ አብ​ር​ሃ​ምን እንደ ፈተ​ነው፥ ይስ​ሐ​ቅ​ንም እንደ ፈተ​ነው፥ ያዕ​ቆ​ብ​ንም የእ​ና​ቱን ወን​ድም የላ​ባን በጎች ሲጠ​ብቅ በሶ​ርያ መስ​ጴ​ጦ​ምያ እንደ ፈተ​ነው አስቡ።

27 እነ​ር​ሱ​ንም በፈ​ተ​ና​ቸ​ውና ልቡ​ና​ቸ​ውን በመ​ረ​መረ ጊዜ እኛን የበ​ደ​ለን አይ​ደ​ለም፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር የሚ​ቀ​ር​ቡ​ትን ሰዎች ይቅር ይላ​ቸው ዘንድ ነው እንጂ፥ ሊያ​ጠ​ፋ​ቸው አይ​ደ​ለ​ምና።”

28 ዖዝ​ያ​ንም አላት፥ “የተ​ና​ገ​ር​ሽ​ውን ሁሉ በበጎ ልቡና ተና​ገ​ርሽ፤ ቃል​ሽ​ንም የሚ​ቃ​ወ​መው የለም።

29 ጥበ​ብሽ የተ​ሰ​ማው ከዛሬ ጀምሮ አይ​ደ​ለ​ምና፥ ከመ​ጀ​መ​ሪ​ያው ዘመ​ንሽ ጀምሮ ሰው ሁሉ በጥ​በ​ብሽ ዐወ​ቀሽ እንጂ፥ የል​ቡ​ናሽ ተፈ​ጥሮ ደግ ነውና።

30 ነገር ግን ሕዝቡ ፈጽ​መው ተጠ​ም​ተ​ዋ​ልና እን​ዳ​ሉን እና​ደ​ርግ ዘንድ ዘበ​ዘ​ቡን፤ ልን​ለ​ው​ጠው የማ​ይ​ቻ​ለ​ንን መሐላ አመ​ጡ​ብን።

31 አሁ​ንም አንቺ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የም​ት​ፈሪ ሴት ነሽና እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ዝና​ምን ያዘ​ን​ም​ልን ዘንድ፥ ኵሬ​ያ​ች​ንም ይመላ ዘንድ፥ እን​ግ​ዲህ ወዲ​ህም እን​ዳ​ን​ጠማ ለም​ኝ​ልን።”

32 ዮዲ​ትም አለ​ቻ​ቸው፥ “ስሙኝ ለልጅ ልጅ የሚ​ነ​ገር ሥራን እሠ​ራ​ለሁ።

33 እና​ንተ ግን በዚች ሌሊት በበሩ ቁሙ፤ እኔም ከብ​ላ​ቴ​ናዬ ጋር እወ​ጣ​ለሁ፤ ሀገ​ራ​ች​ንን አሳ​ል​ፈን ለጠ​ላ​ቶ​ቻ​ችን እን​ሰ​ጣ​ለን በም​ት​ሉ​በት በእ​ነ​ዚ​ያም ወራ​ቶች የእ​ስ​ራ​ኤል አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእጄ ይረ​ዳል።

34 እና​ንተ ግን የም​ሠ​ራ​ውን ሥራ አት​መ​ር​ም​ሩኝ፤ እኔ የም​ሠ​ራው ሥራ እስ​ኪ​ፈ​ጸም ድረስ አል​ነ​ግ​ራ​ች​ሁ​ምና።”

35 ዖዝ​ያ​ንና አለ​ቆ​ቻ​ቸ​ውም፥ “በሰ​ላም ሂጂ፤ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በፊ​ትሽ ይሁን፤ ጠላ​ቶ​ቻ​ች​ን​ንም ይበ​ቀል” አሏት።

36 ተመ​ል​ሰ​ውም ወደ ባል​ን​ጀ​ሮ​ቻ​ቸው ሄዱ።

跟着我们:



广告