Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 7 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የቤ​ጤ​ልዋ መከ​በብ

1 በማ​ግ​ሥ​ቱም ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ወደ ቤጤ​ልዋ ይጓዙ ዘንድ፥ ቀድ​መ​ውም የአ​ን​ባ​ዎ​ቹን መግ​ቢያ ይይ​ዙና የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች ይዋ​ጓ​ቸው ዘንድ ከእ​ርሱ ጋራ የተ​ሰ​ለፉ ጭፍ​ሮ​ቹ​ንና ወገ​ኖ​ቹን ሁሉ አዘ​ዛ​ቸው።

2 በዚ​ያም ቀን ጽኑ​ዓን አር​በ​ኞች የሆኑ ኀይ​ለ​ኞች ሰዎች ሁሉ ወረዱ፤ እነ​ዚ​ያም ጓዝ ከሚ​ጠ​ብቁ ካል​ከ​በቡ ከብዙ አር​በ​ኞች ሰዎች በቀር መቶ ሰባ ሺህ እግ​ረ​ኞ​ችና ዐሥራ ሁለት ሺህ ፈረ​ሰ​ኞች ነበሩ።

3 በቤ​ጤ​ልዋ አጠ​ገብ፥ በአ​ው​ሎን በው​ኃው ምንጭ አጠ​ገብ ሰፈሩ፤ የሰ​ፈ​ራ​ቸ​ውም አቆ​ል​ቋዩ እስከ ዶታ​ይ​ምና ቤጤ​ልዋ ድረስ፥ ወር​ዱም በአ​ሴ​ዴ​ራ​ሎም አን​ጻር ከቤ​ጤ​ልዋ እስከ ቅያ​ሞስ ደረሰ።

4 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ብዛ​ታ​ቸ​ውን በአዩ ጊዜ እጅግ ደነ​ገጡ፤ እርስ በር​ሳ​ቸ​ውም፥ “እነ​ዚህ ሰዎች ዛሬ ምድ​ርን ሁሉ ይሸ​ፍ​ኗ​ታል፤ ተራ​ራም ቢሆን፥ ኮረ​ብ​ታም ቢሆን፥ ቈላም ቢሆን ብዛ​ታ​ቸ​ውን የሚ​ችል የለም” ተባ​ባሉ።

5 ሁሉም መሣ​ሪ​ያ​ቸ​ውን ያዙ፤ ባን​ባ​ቸ​ውም እሳት አነ​ደዱ፤ በዚ​ያ​ችም ሌሊት ሁሉ ሲጠ​ብቁ አደሩ።

6 በሁ​ለ​ተ​ኛ​ውም ቀን ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ በቤ​ጤ​ልዋ ባሉ በእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ፊት ፈረ​ሶ​ቹን ጫነ።

7 የከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸ​ውን መግ​ቢያ ያዩ ዘንድ፥ የው​ኃ​ቸ​ው​ንም ምንጭ ይከቡ ዘንድ፥ ወደ​ዚ​ያም አር​በ​ኞች ሰዎች ቀድ​መው ይደ​ር​ሱና ይከቡ ዘንድ ጕበ​ኞ​ችን ላከ።

8 እር​ሱም ከሠ​ራ​ዊቱ ጋር ፈጥኖ ሄደ፤ አር​በ​ኞች የሆኑ የኤ​ሳው ልጆች አለ​ቆ​ችም ሁሉ የሞ​ዓብ ወገ​ኖች ሹሞች ሁሉና የባ​ሕር ዙሪያ ገዢ​ዎች ወደ እርሱ መጡ።

9 እን​ዲ​ህም አሉት፥ “አቤቱ በሠ​ራ​ዊ​ትህ ላይ ጥፋት እን​ዳ​ይ​ሆን ቃላ​ች​ንን ስማ።

10 እነ​ዚህ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ወገ​ኖች በሚ​ኖ​ሩ​ባ​ቸው አን​ባ​ዎ​ቻ​ቸ​ውና ኮረ​ብ​ታ​ዎ​ቻ​ቸው ነው እንጂ በጦ​ራ​ቸው የሚ​ተ​ማ​መኑ አይ​ደ​ሉም፤ ለአ​ን​ባ​ዎ​ቻ​ቸው መውጫ የላ​ቸ​ው​ምና፤

11 አቤቱ አሁ​ንም በሰ​ልፍ ሥር​ዐት አቷ​ጋ​ቸው፤ ከሠ​ራ​ዊ​ትህ አንድ ሰው ስንኳ የሚ​ሞት አይ​ኑር።

12 ነገር ግን አንተ ከሠ​ራ​ዊ​ትህ ጋር በሰ​ፈር ጠብ​ቃ​ቸው፤ አሽ​ከ​ሮ​ች​ህና የሠ​ራ​ዊ​ትህ አር​በ​ኞች ሁሉ ከተ​ራ​ራው በታች የሚ​ፈ​ልቅ የው​ኃ​ቸ​ውን ምን​ጮች ሁሉ አጽ​ን​ተው ይጠ​ብቁ።

13 በቤ​ጤ​ልዋ የሚ​ኖሩ ሰዎች ሁሉ ከዚህ ውኃ ስለ​ሚ​ቀዱ ውኃ ጥም ይገ​ድ​ላ​ቸ​ዋል፤ ሀገ​ራ​ቸ​ው​ንም ለአ​ንተ ያሰ​ገ​ዛሉ፤ ሠራ​ዊ​ቶ​ቻ​ች​ንና እኛም ላን​ባ​ቸው ቅርብ ወደ ሆነ ቦታ ወደ ኮረ​ብ​ታ​ቸ​ውም ራስ እን​ወ​ጣ​ለን ካን​ባ​ቸው አንድ ሰው ስንኳ የሚ​ወጣ እን​ዳ​ይ​ኖር በዚያ ሰፍ​ረን እን​ጠ​ብ​ቃ​ቸ​ዋ​ለን።

14 እነ​ርሱ፥ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ልጆ​ቻ​ቸ​ውም በረ​ኃብ ይጠ​ፋሉ፤ ሳይ​ዋ​ጓ​ቸ​ውም ባገ​ራ​ቸው ጎዳና ይወ​ድ​ቃሉ።

15 ከድ​ተ​ዋ​ልና፥ በሰ​ላ​ምም አል​ተ​ቀ​በ​ሉ​ህ​ምና ጽኑ በቀ​ልን ትበ​ቀ​ላ​ቸ​ዋ​ለህ።”

16 በሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ፊትና በሠ​ራ​ዊቱ ሁሉ ፊት ቃላ​ቸው ደስ አሰኘ፤ እንደ ተና​ገ​ሩም ያደ​ርጉ ዘንድ አዘዘ።

17 የአ​ሞን ልጆች ሠራ​ዊ​ትም ተጓዙ፤ አም​ስት ሺህ የሚ​ሆኑ የአ​ሦር ሠራ​ዊ​ትም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ነበሩ፤ በአ​ው​ሎ​ኒም ሰፈሩ፤ የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ልጆች ምን​ጮ​ችና ውኃ​ቸ​ውን አስ​ቀ​ድ​መው ያዙ።

18 የኤ​ሳ​ውና የአ​ሞን ልጆ​ችም ወጥ​ተው በዶ​ታ​ይም አን​ጻር ባሉ ተራ​ሮች ሰፈሩ፤ ከእ​ነ​ር​ሱም በም​ኩር ወንዝ ባለ በኩሲ አጠ​ገብ ባለ በኤ​ቄ​ሬ​ቢን አን​ጻር ወደ ደቡ​ብና ወደ ምሥ​ራቅ ሰዎ​ችን ላኩ። የቀ​ሩት የአ​ሦር ሠራ​ዊ​ቶች ግን በም​ድረ በዳ ሰፈሩ፤ ሀገ​ሩ​ንም ሁሉ አለ​በ​ሱት፤ ከዚ​ህም በኋላ ጓዛ​ቸ​ውን ከእ​ነ​ርሱ የሚ​በዛ የሌለ ሠራ​ዊ​ታ​ቸ​ው​ንና ብዙ ገን​ዘ​ባ​ቸ​ውን አጓዙ።


የእ​ስ​ራ​ኤ​ላ​ው​ያን መጨ​ነቅ

19 ጠላ​ቶ​ቻ​ቸው ስለ ከበ​ቧ​ቸው፥ ከመ​ካ​ከ​ላ​ቸ​ውም መውጫ ስለ​ሌ​ላ​ቸው ሰው​ነ​ታ​ቸው ተጨ​ን​ቃ​ለ​ችና የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ወደ አም​ላ​ካ​ቸው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጮኹ።

20 አሦ​ራ​ው​ያ​ንም ከሠ​ራ​ዊ​ቶ​ቻ​ቸው ሁሉ ጋር አር​በ​ኞ​ቻ​ቸ​ውም በፈ​ረ​ሶ​ችና በሰ​ረ​ገላ የተ​ቀ​መጡ ሰዎ​ችም ከበ​ዋ​ቸው ሠላሳ አራት ቀን ተቀ​መጡ፤ በቤ​ጤ​ልዋ የሚ​ኖሩ ሰዎ​ችም በዕ​ቃ​ቸው ያለ ውኃ​ቸው ሁሉ አለቀ።

21 የሚ​ጠ​ጡት ላንድ ቀን የሚ​ያ​ረ​ካ​ቸው ውኃ አል​ነ​በ​ራ​ቸ​ውም፤ በመ​ስ​ፈ​ሪያ እየ​መ​ጠኑ ወደ መጠ​ጣ​ትም ተመ​ለሱ።

22 ልጆ​ቻ​ቸ​ውና ሚስ​ቶ​ቻ​ቸው፥ ጐል​ማ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም ተጨ​ነቁ፤ በውኃ ጥም አለቁ፤ በከ​ተ​ማ​ውም አደ​ባ​ባ​ይና በበሩ ጎዳና ወደቁ፤ ከዚ​ህም በኋላ ምንም ኀይል አል​ነ​በ​ራ​ቸ​ውም።

23 ሕዝቡ ሁሉ፥ ጐል​ማ​ሶ​ችና የከ​ተ​ማው አለ​ቆ​ችም፥ ልጆ​ችና ሴቶ​ችም ወደ ዖዝ​ያን ተሰ​በ​ሰቡ፤ ቃላ​ቸ​ው​ንም አሰ​ም​ተው ጮኹ። በአ​ለ​ቆ​ቻ​ቸ​ውም ፊት እን​ዲህ አሉ፦

24 “በእኛ ላይ ታላቅ ጉዳ​ትን ታደ​ር​ሱ​ብን ዘንድ ከአ​ሦር ሰዎች አሽ​ከ​ሮች ጋራ በሰ​ላም በጎ ነገር ባል​ተ​ና​ገ​ራ​ችሁ በእ​ና​ን​ተና በእኛ መካ​ከል እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ይፍ​ረድ።

25 አሁ​ንም የሚ​ረ​ዳን አጣን፤ በፊ​ታ​ቸ​ውም በውኃ ጥምና በጽኑ ጥፋት እን​ጠፋ ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በእ​ጃ​ቸው ጣለን።

26 አሁ​ንም ተገ​ዙ​ላ​ቸው፤ ይዘ​ር​ፉም ዘንድ ከተ​ሞ​ቻ​ች​ሁን ሁሉ ለሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ወገ​ኖ​ችና ሠራ​ዊት አሳ​ል​ፋ​ችሁ ስጧ​ቸው።

27 ሰው​ነ​ታ​ችን እን​ድ​ት​ድን፥ የል​ጆ​ቻ​ች​ን​ንም ሞት በዐ​ይ​ኖ​ቻ​ችን እን​ዳ​ናይ በውኃ ጥም ከም​ን​ሞት ቢዘ​ር​ፉ​ንና ብን​ገ​ዛ​ላ​ቸው ይሻ​ለ​ና​ልና፥ የሚ​ስ​ቶ​ቻ​ች​ንና የል​ጆ​ቻ​ችን ሰው​ነ​ትም አል​ቃ​ለ​ችና።

28 እነሆ፥ ዛሬ በዚች ቀን ይህን ነገር እን​ዳ​ታ​ደ​ርጉ ሰማ​ይ​ንና ምድ​ርን እን​ዳ​ባ​ቶ​ቻ​ችን ኀጢ​አ​ትና እንደ ኀጢ​አ​ታ​ችን የሚ​ፈ​ር​ድ​ብን ያባ​ቶ​ቻ​ችን አም​ላክ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን እና​ዳ​ኝ​ባ​ች​ኋ​ለን።”

29 በማ​ኅ​በ​ሩም መካ​ከል ጽኑ ልቅሶ ሆነ፤ ሁሉም በአ​ን​ድ​ነት አለ​ቀሱ፤ ቃላ​ቸ​ው​ንም አሰ​ም​ተው ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጮኹ።

30 ዖዝ​ያ​ንም አላ​ቸው፥ “ወን​ድ​ሞ​ቻ​ችን ሆይ! ሁል​ጊዜ በመ​ከ​ራው የሚ​ጥ​ለን አይ​ደ​ለ​ምና ፈጣ​ሪ​ያ​ችን እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቸር​ነ​ቱን እስ​ኪ​መ​ል​ስ​ልን ድረስ እመኑ፤ ዳግ​መ​ኛም አም​ስት ቀን ታገሡ።

31 እነ​ዚህ አም​ስት ቀኖች ካለፉ በኋላ ረድ​ኤቱ ካል​መ​ጣ​ልን እንደ ተና​ገ​ራ​ች​ሁት እና​ደ​ር​ጋ​ለን።”

32 ሕዝ​ቡ​ንም ወደ​የ​ሰ​ፈ​ራ​ቸው በተ​ና​ቸው፤ እነ​ር​ሱም ወደ ከተ​ማ​ቸው ግን​ብና አንባ ሄዱ፤ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንና ልጆ​ቻ​ቸ​ው​ንም ወደ ቤታ​ቸው ላኩ፤ በከ​ተ​ማም ፈጽ​መው የተ​ጨ​ነቁ ነበሩ።

跟着我们:



广告