Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 6 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


አክ​ዮር ለእ​ስ​ራ​ኤል ተላ​ልፎ መሰ​ጠቱ

1 ከዚህ በኋላ በሸ​ን​ጎው ዙሪያ ያሉ እነ​ዚያ ሰዎች ዝም ባሉ ጊዜ የአ​ሦር ሠራ​ዊት አለቃ ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ አክ​ዮ​ርን በፍ​ል​ስ​ጥ​ኤም ወገ​ኖ​ችና በሞ​ዓብ ልጆች ሁሉ ፊት እን​ዲህ አለው፦

2 “አንተ የኤ​ፍ​ሬም ምን​ደኛ አክ​ዮር! ዛሬ ትን​ቢት ትና​ገ​ር​ልን ዘንድ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ያጸ​ና​ቸ​ዋ​ልና የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች አት​ው​ጓ​ቸው ትለን ዘንድ አንተ ማን ነህ? ያለ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርስ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ማን ነው?

3 እርሱ ኀያ​ላ​ኑን ልኮ ከገጸ ምድር ፈጽሞ ያጠ​ፋ​ቸ​ዋል፤ አም​ላ​ካ​ቸ​ውም አያ​ድ​ና​ቸ​ውም፤ እኛም የና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ባሮች እንደ አንድ ሰው እና​ጠ​ፋ​ቸ​ዋ​ለን፤ በእ​ነ​ርሱ እን​ረ​ግ​ጣ​ቸ​ዋ​ለ​ንና የፈ​ረ​ሶ​ቻ​ች​ን​ንም ኀይል ሊቋ​ቋሙ አይ​ች​ሉም።

4 ተራ​ሮ​ቻ​ቸ​ውም በደ​ማ​ቸው ይሰ​ክ​ራሉ፤ የል​ጆ​ቻ​ቸ​ውም ሬሳ ይበ​ዛል፤ የዓ​ለሙ ሁሉ ጌታ ንጉሡ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር አጠ​ፋ​ቸ​ዋ​ለሁ ብሏ​ልና ቃሉ ሐሰት እን​ዳ​ይ​ሆን ከዚህ ዓለም ፈጽ​መው ይጠ​ፋሉ እንጂ በፊ​ታ​ችን በእ​ግ​ራ​ቸው አይ​ቆ​ሙም።

5 “ዛሬ በኀ​ጢ​አ​ትህ ይህን የተ​ና​ገ​ርህ የአ​ሞን ምን​ደኛ አክ​ዮር፥ አንተ ግን ከግ​ብፅ ሀገር የወጡ እስ​ራ​ኤ​ልን ተበ​ቅዬ እስ​ካ​ጠ​ፋ​ቸው ድረስ ከዚህ ቀን ጀምሮ እን​ግ​ዲህ ወዲህ ፊቴን አታ​የ​ውም።

6 የዚ​ያን ጊዜ የጭ​ፍ​ራ​ዎ​ችና የወ​ገ​ኖች ጦር በጎ​ንህ ይገ​ባል፤ ከሬ​ሳ​ዎ​ቻ​ቸ​ውም ጋራ ትወ​ድ​ቃ​ለህ።

7 በተ​መ​ለ​ስ​ሁም ጊዜ ባሮች ወደ አን​ባ​ቸው ይወ​ስ​ዱ​ሃል፤ ባቀ​በ​ቱም ካሉ ከተ​ሞ​ቻ​ቸው ባን​ዲት ከተማ ያኖ​ሩ​ሃል።

8 እስ​ካ​ጠ​ፋ​ቸ​ውም ድረስ አይ​ገ​ድ​ሉ​ህም።

9 እን​ደ​ማ​ን​ች​ላ​ቸው በል​ብህ ትታ​መ​ና​ለ​ህና ፊትህ አይ​ው​ደቅ፤ እኔ ተና​ግ​ሬ​አ​ለ​ሁና፤ ከቃ​ሌም የሚ​ወ​ድቅ የለ​ምና።”

10 ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም በፊቱ በድ​ን​ኳኑ ውስጥ የሚ​ቆሙ አሽ​ከ​ሮ​ቹን አክ​ዮ​ርን ይዘው ወደ ቤጤ​ልዋ ይወ​ስ​ዱት ዘንድ፥ ለእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች እር​ሱን ይሰ​ጧ​ቸው ዘንድ አዘ​ዛ​ቸው።

11 አሽ​ከ​ሮ​ቹም ይዘው ከሰ​ፈሩ ውጭ ወደ ምድረ በዳ ወሰ​ዱት፤ ከም​ድረ በዳ​ውም መካ​ከል ወደ ተራ​ራ​ማው ሀገር ሄዱ፤ ከዚ​ህም በኋላ በቤ​ጤ​ልዋ በታች ወዳሉ ምን​ጮች ደረሱ።

12 የዚ​ያ​ችም ሀገር ሰዎች ባዩ​አ​ቸው ጊዜ መሣ​ሪ​ያ​ቸ​ውን ይዘው ከከ​ተማ ወደ ተራ​ራው ራስ ሄዱ። ወን​ጭፍ የያዙ ሰዎ​ችም ሁሉ መግ​ቢ​ያ​ውን ጠበቁ፤ በላ​ያ​ቸ​ውም መርግ ጣሉ።

13 የአ​ክ​ዮ​ር​ንም እግር ብረት ፈቱት፤ በተ​ራ​ራ​ውም በታች አሰ​ሩት፤ በዚ​ያም በተ​ራ​ራው በታች ጣሉት፤ ትተ​ው​ትም ወደ ጌታ​ቸው ተመ​ለሱ።

14 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ከአ​ን​ባ​ቸው ወር​ደው ወደ እርሱ ሄዱ፤ ፈት​ተ​ውም ወደ ቤጤ​ልዋ ወሰ​ዱት።

15 በዚ​ያም ወራት የከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸው አለ​ቆች በነ​በ​ሩት ከነ​ገደ ስም​ዖን በሚካ ልጅ ኦዝ​ያ​ስና በጎ​ቶ​ንያ ልጅ በክ​ብ​ሪስ፥ በመ​ል​ክ​ያል ልጅ በከ​ር​ሚ​ስም ዘንድ አስ​ቀ​መ​ጡት።

16 በከ​ተ​ሞ​ቻ​ቸ​ውም ያሉ አለ​ቆ​ችን ሁሉ ጠሩ፤ ሴቶ​ቻ​ቸ​ውና ጐል​ማ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም ሁሉ ሮጠው ወደ ሸን​ጓ​ቸው ሄዱ፤ አክ​ዮ​ር​ንም በሁሉ መካ​ከል አቆ​ሙት፤ ኦዝ​ያ​ስም የተ​ደ​ረ​ገ​ውን ሁሉ ጠየ​ቀው።

17 እንደ ዶለ​ቱና በአ​ሦር ሠራ​ዊት አለ​ቆች መካ​ከል ነገ​ራ​ቸ​ውን ሁሉ እንደ ተና​ገሩ፥ ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም በእ​ስ​ራ​ኤል ወገ​ኖች ላይ በት​ዕ​ቢት እንደ ተና​ገረ መልሶ የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒ​ስን ነገር ሁሉ ነገ​ራ​ቸው።

18 ሕዝ​ቡም ሁሉ በግ​ን​ባ​ራ​ቸው ወድ​ቀው ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰገዱ፤ እን​ዲ​ህም እያሉ ጸለዩ፦

19 “አቤቱ የሰ​ማይ አም​ላክ ሆይ፥ ትዕ​ቢ​ታ​ቸ​ውን ተመ​ል​ከት፤ የወ​ገ​ኖ​ቻ​ች​ን​ንም መከራ አይ​ተህ ይቅር በል፤ በዚ​ችም ቀን ወደ መቅ​ደ​ስህ ተመ​ል​ከት።”

20 አክ​ዮ​ር​ንም ደስ አሰ​ኙት፤ ፈጽ​መ​ውም አከ​በ​ሩት።

21 ኦዝ​ያ​ስም ከተ​ሰ​በ​ሰ​ቡ​በት ወስዶ ወደ ቤቱ አገ​ባው፤ ለሽ​ማ​ግ​ሌ​ዎ​ችም በዓ​ልን አደ​ረጉ፤ ይረ​ዳ​ቸ​ውም ዘንድ የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን አም​ላክ በዚ​ያች ሌሊት ሁሉ ለመ​ኑት።

跟着我们:



广告