Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 5 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ በእ​ስ​ራ​ኤል ላይ ለመ​ዝ​መት የጠ​ራው ስብ​ሰባ

1 “የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች ለሰ​ልፍ ተዘ​ጋጁ፤ የኮ​ረ​ብ​ታ​ቸ​ው​ንም በሮች ዘጉ። የአ​ም​ባ​ው​ንም ራሶች አጠሩ፤ መን​ገ​ዱ​ንም ጐፃ​ጕፅ አደ​ረጉ” ብለው ለአ​ሦር ሠራ​ዊት አለቃ ለሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ነገ​ሩት።

2 እር​ሱም ፈጽሞ ተቈጣ፤ የሞ​አ​ብን አለ​ቆ​ችና የአ​ሞ​ንን ሹሞች፥ በባ​ሕር ዙሪያ ያሉ ገዢ​ዎ​ች​ንም ጠራ​ቸው።

3 እን​ዲ​ህም አላ​ቸው፥ “የከ​ነ​ዓን ልጆች ሆይ! ንገ​ሩኝ፤ በተ​ራ​ሮች የሚ​ኖሩ እነ​ዚህ ወገ​ኖች ምን​ድን ናቸው? በከ​ተ​ሞች የሚ​ኖሩ፥ ሠራ​ዊ​ታ​ቸ​ውም ብዙ የሆኑ እኒ​ያስ ወገ​ኖች ምን​ድን ናቸው? ጽና​ታ​ቸ​ውስ ምን ያህል ነው? በእ​ነ​ር​ሱስ ላይ የነ​ገሠ ንጉሥ ማን ነው? ወይስ ሹማ​ቸው? ወይስ አለ​ቃ​ቸው ማን ነው?

4 በም​ዕ​ራብ ከሚ​ኖሩ ሰዎች ሁሉ ጋር ይቀ​በ​ሉኝ ዘንድ እን​ዴት አል​መ​ጡም?”


የአ​ክ​ዮር ንግ​ግር

5 የአ​ሞን ልጆች ሹም አክ​ዮ​ርም እን​ዲህ አለ፥ “ከእኔ ከባ​ር​ያህ አን​ደ​በት ይህን ነገር ስማ፤ ከእኔ ከባ​ሪ​ያህ አን​ደ​በት ሐሰት ነገር አይ​ወ​ጣ​ምና፥ በእ​ነ​ዚህ አን​ባ​ዎች፥ በአ​ቅ​ራ​ቢ​ያ​ህም ስለ​ሚ​ኖሩ ስለ​እ​ነ​ዚህ ወገ​ኖች እው​ነት ነገ​ርን እነ​ግ​ር​ሃ​ለሁ።

6 እነ​ዚህ ወገ​ኖች ከከ​ላ​ው​ዴ​ዎን መጡ።

7 በከ​ላ​ው​ዴ​ዎን ሀገር የሚ​ኖሩ የአ​ባ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን ጣዖ​ቶች ያመ​ልኩ ዘንድ አል​ወ​ደ​ዱ​ምና አስ​ቀ​ድ​መው በመ​ስ​ጴ​ጦ​ምያ ይኖሩ ነበረ።

8 የወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸ​ው​ንም መን​ገድ ትተ​ዋ​ልና ላወ​ቁት ከጣ​ዖ​ቶ​ቻ​ቸው ፊት ላወ​ጣ​ቸው ለሰ​ማይ አም​ላክ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ሰግ​ደ​ዋ​ልና ወደ መስ​ጴ​ጦ​ምያ ሸሽ​ተው በዚያ ብዙ ዘመን ኖሩ።

9 ፈጣ​ሪ​ያ​ቸ​ውም ከተ​ሰ​ደ​ዱ​በት ሀገር ይወ​ጡና ወደ ከነ​ዓን ይሄዱ ዘንድ አዘ​ዛ​ቸው፤ በዚ​ያም ብዙ ዘመን ኖሩ፤ ብር​ንና ወር​ቅን፥ ብዙ ከብ​ቶ​ች​ንም ፈጽ​መው አበዙ።

10 ረኃብ በከ​ነ​ዓን ሀገር ሁሉ ጸን​ት​ዋ​ልና ወደ ግብፅ ወረዱ፤ በዚ​ያም እየ​ተ​መ​ገቡ ኖሩ፤ በዚ​ያም በዝ​ተው ሞሉ፤ ለወ​ገ​ኖ​ቻ​ቸ​ውም ቍጥር አል​ነ​በ​ራ​ቸ​ውም።

11 የግ​ብፅ ንጉ​ሥም በጠ​ላ​ት​ነት ተነ​ሣ​ባ​ቸው፤ ተተ​ነ​ኰ​ለ​ባ​ቸ​ውም፤ መከ​ራም አጸ​ና​ባ​ቸው፤ ጡብ በማ​ሠ​ራ​ትም ገዛ​ቸው፤ ባሮ​ችም አደ​ረ​ጋ​ቸው።

12 ወደ አም​ላ​ካ​ቸ​ውም ጮኹ፤ እር​ሱም መድ​ኀ​ኒት በሌ​ለው መቅ​ሠ​ፍት የግ​ብፅ ሀገ​ርን ሁሉ አጠፋ፤ ግብ​ፃ​ው​ያ​ንም ከፊ​ታ​ቸው አስ​ወ​ጡ​አ​ቸው።

13 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በፊ​ታ​ቸው የኤ​ር​ት​ራን ባሕር አደ​ረ​ቃት።

14 ወደ ሲና ተራ​ራና ቃዴስ በርኔ ወሰ​ዳ​ቸው፤ በም​ድረ በዳ የሚ​ኖ​ሩ​ት​ንም ሁሉ አወ​ጣ​ቸው።

15 በአ​ሞ​ራ​ው​ያን ሀገ​ርም ኖሩ፤ የሐ​ሴ​ቦ​ን​ንም ሰዎች ሁሉ በኀ​ይሉ አጠፋ ዮር​ዳ​ኖ​ስ​ንም ተሻ​ግ​ረው ተራ​ራ​ማ​ውን ሀገር ሁሉ ወረሱ።

16 ከና​ኔ​ዎ​ንን፥ ፌር​ዜ​ዎ​ንን፥ ኢያ​ቡ​ሴ​ዎ​ንን፥ ሴኬ​ምን፥ ጌር​ጌ​ሴ​ዎ​ን​ንም ሁሉ ከፊ​ታ​ቸው አስ​ወ​ጣ​ቸው፤ በዚ​ያም ብዙ ዘመን ኖሩ።

17 “በፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸ​ውም ፊት ባል​በ​ደሉ ጊዜ መል​ካም ነገር ሁሉ ሆነ​ላ​ቸው፤ በደ​ልን የሚ​ጠላ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ከእ​ነ​ርሱ ጋር ነበ​ረና።

18 ያዘ​ዛ​ቸ​ውን ሥር​ዐት በተዉ ጊዜ ግን ፈጽሞ በብዙ ጦር አጠ​ፋ​ቸው፤ ወደ ባዕድ ሀገ​ርም ተማ​ረኩ፤ የፈ​ጣ​ሪ​ያ​ቸው ማደ​ሪያ ቤተ መቅ​ደ​ስም ፈረሰ፤ ምድረ በዳም ሆነ፤ ከተ​ሞ​ቻ​ቸ​ው​ንም ጠላ​ቶ​ቻ​ቸው ያዙ​ባ​ቸው።

19 ዛሬ ግን ወደ ፈጣ​ሪ​ያ​ቸው ተመ​ለሱ፤ ከተ​በ​ተ​ኑ​በ​ትም ሀገር ከዚያ ተሰ​በ​ሰቡ፤ ቤተ መቅ​ደስ ባለ​በት በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም ኖሩ፤ ምድረ በዳም ነውና በተ​ራ​ራው ኖሩ።

20 አሁ​ንም አቤቱ ጌታዬ እነ​ዚህ ወገ​ኖች በደል እን​ዳ​ለ​ባ​ቸው፥ ፈጣ​ሪ​ያ​ቸ​ው​ንም በድ​ለው እንደ ሆነ ይህ መሰ​ና​ክ​ላ​ቸው ነውና አንድ ጊዜ እና​ረ​ጋ​ግጥ፤ ከዚያ በኋላ ወጥ​ተን እን​ዋ​ጋ​ቸ​ዋ​ለን።

21 በእ​ነ​ዚህ ወገ​ኖች በደል ከሌ​ለ​ባ​ቸው ግን ጌታዬ እለ​ፋ​ቸው፤ እነሆ ጌታ​ቸው ያጸ​ና​ቸው ይሆ​ናል፤ ወይም አም​ላ​ካ​ቸው ይቆ​ም​ላ​ቸው ይሆ​ናል፤ እኛም በሀ​ገሩ ሁሉ ኀፍ​ረት እን​ሆ​ና​ለን።”

22 ከዚህ በኋላ አክ​ዮር ይህን ነገር ተና​ግሮ በጨ​ረሰ ጊዜ በሰ​ፈሩ ዙሪያ የቆሙ ወገ​ኖች ሁሉ አን​ጐ​ራ​ጐሩ፤ የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ሹሞች፥ በባ​ሕር ዙሪ​ያና በሞ​ዓብ የሚ​ኖሩ ሰዎ​ችም ሁሉ “አክ​ዮ​ርን እን​ግ​ደ​ለው” አሉ።

23 “ከጽኑ አር​በኛ ጋር ይዋጉ ዘንድ ብር​ታ​ትና ኀይል የሌ​ላ​ቸ​ውን ወገ​ኖች የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ልጆች የም​ን​ፈ​ራ​ቸው አይ​ደ​ለም።

24 ስለ​ዚህ ግን ጌታ​ችን ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ሆይ፥ እን​ዝ​መት፤ እነ​ር​ሱም ለጭ​ፍ​ራ​ዎ​ችህ ሁሉ ምግብ ይሆ​ናሉ” አሉ።

跟着我们:



广告