Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 4 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


አይ​ሁድ ራሳ​ቸ​ውን ለመ​ከ​ላ​ከል ያደ​ረ​ጉት ዝግ​ጅት

1 በይ​ሁዳ የሚ​ኖሩ የእ​ስ​ራ​ኤል ልጆች የአ​ሦር ንጉሥ የና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ቢት​ወ​ደድ ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ በአ​ሕ​ዛብ ያደ​ረ​ገ​ውን ሁሉ፥ አው​ራ​ጃ​ዎ​ቻ​ቸ​ውን ሁሉ እን​ዳ​ጠፋ፥ እነ​ር​ሱ​ንም እን​ዳ​ጠ​ፋ​ቸው ሰሙ።

2 ከመ​ቅ​ረ​ቡም የተ​ነሣ ስለ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና ስለ አም​ላ​ካ​ቸው ስለ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ቤተ መቅ​ደስ ፈጽ​መው ፈሩ።

3 ከይ​ሁዳ የተ​መ​ረጡ ወገ​ኖ​ችም ሁሉ በቅ​ርቡ ከም​ርኮ ከተ​መ​ለሱ በኋላ ተሰ​ብ​ስ​በው ነበ​ርና ምሥ​ዋ​ዑ​ንና ንዋየ ቅድ​ሳ​ቱን፥ ቤተ መቅ​ደ​ሱ​ንም ከረ​ከሰ በኋላ አነ​ጹት።

4 ስለ​ዚ​ህም ወደ ሰማ​ርያ አው​ራ​ጃ​ዎ​ችና ወደ ቆና፥ ወደ ቤቶ​ሮ​ንና ወደ ቤል​ሜን፥ ወደ ኢያ​ሪ​ኮና ወደ ኮባ፥ ወደ ኤሦ​ራና ወደ ሳሌም ሸለቆ ሁሉ ላኩ።

5 ከፍ ያሉ የተ​ራ​ራ​ዎ​ቻ​ቸ​ው​ንም ጫፎች ያዙ። በሚ​ኖ​ሩ​ባ​ቸው መን​ደ​ሮ​ችም መሸጉ። አዝ​መ​ራ​ቸ​ውም ቀደም ብሎ ተሰ​ብ​ስቦ ነበ​ርና ለጦ​ር​ነት ስን​ቅን አዘ​ጋጁ።

6 በዚ​ያም ወራት በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሚ​ኖር የካ​ህ​ናቱ አለቃ ኢዮ​አ​ቄም በዶ​ታ​ይም አጠ​ገብ ባለች ምድረ በዳ፥ በኤ​ስ​ድ​ራ​ሎም አን​ጻር ባለች በቤ​ጦ​ሜ​ስ​ቴ​ምና በቤ​ጤ​ልዋ ለሚ​ኖሩ ሰዎች ጻፈ።

7 በዚ​ያም በይ​ሁዳ ላይ መግ​ቢያ ስለ​አ​ለና መግ​ቢ​ያ​ውም ለሁ​ለት ሰዎች መተ​ላ​ለ​ፊያ ብቻ ነው እንጂ ጠባብ ስለ ሆነ የሚ​ወ​ጡ​ትን ለመ​ከ​ላ​ከል የአ​ን​ባ​ዎ​ቹን መግ​ቢያ አጽ​ን​ታ​ችሁ ጠብቁ ብሎ ጻፈ።


የእ​ስ​ራ​ኤል ጸሎት

8 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ታላቁ ካህን ኢዮ​አ​ቄ​ምና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሚ​ኖሩ የእ​ስ​ራ​ኤል ወገ​ኖች አለ​ቆች ሁሉ እን​ዳ​ዘ​ዙ​አ​ቸው አደ​ረጉ።

9 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ልጆች ከፍ ባለ ቃል ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጮኹ፤ ሰው​ነ​ታ​ቸ​ው​ንም በጽኑ ኀዘን አሳ​ዘኑ።

10 እነ​ር​ሱም ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውና ልጆ​ቻ​ቸው፥ ከብ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም፥ ምን​ደ​ኛ​ውና ስደ​ተ​ኛው ሁሉ፥ በዋ​ጋም የተ​ገ​ዛው ሁሉ ማቅ ለብ​ሰው አለ​ቀሱ።

11 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ወገ​ኖች ሁሉ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውና በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም የሚ​ኖሩ ልጆ​ቻ​ቸ​ውም በቤተ መቅ​ደስ ደጃፍ ወደቁ፤ በራ​ሳ​ቸ​ውም ትቢያ ነሰ​ነሱ፤ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ፊት ማቃ​ቸ​ውን አነ​ጠፉ፤ መሠ​ዊ​ያ​ው​ንም ማቅ አለ​በሱ።

12 ልጆ​ቻ​ቸ​ውን እን​ዳ​ይ​ነ​ጠቁ፥ ሚስ​ቶ​ቻ​ቸ​ውን እን​ዳ​ይ​ማ​ረኩ፥ የር​ስ​ታ​ቸው ከተ​ሞ​ችም እን​ዳ​ይ​ጠፉ፥ መቅ​ደ​ሳ​ቸ​ው​ንም እን​ዳ​ያ​ረ​ክሱ፥ ለአ​ሕ​ዛ​ብም መዘ​በቻ እን​ዳ​ያ​ደ​ር​ጉት ወደ እስ​ራ​ኤል አም​ላክ በአ​ን​ድ​ነት ፈጽ​መው ጮኹ።

13 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም መከ​ራ​ቸ​ውን አይቶ ልመ​ና​ቸ​ውን ሰማ፤ ሕዝ​ቡም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌ​ምና በይ​ሁዳ ሁሉን በሚ​ችል በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መቅ​ደስ ፊት ብዙ ቀን ጾሙ።

14 በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ፊት የሚ​ቆሙ ታላቁ ካህን ኢዮ​አ​ቄ​ምና ካህ​ናቱ፥ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሥራ የሚ​ሠሩ ሰዎች በወ​ገ​ባ​ቸው ማቅ ታጠቁ፤ የዘ​ወ​ት​ሩን መሥ​ዋ​ዕት፥ የስ​እ​ለ​ቱ​ንና ሕዝቡ በፈ​ቃድ የሚ​ያ​ቀ​ር​ቡ​ትን መሥ​ዋ​ዕት አገቡ።

15 በራ​ሳ​ቸ​ውም ዐመድ ነሰ​ነሱ፤ በፍ​ጹም ኀይ​ላ​ቸ​ውም ወደ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ጮኹ፤ “የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ወገን በም​ሕ​ረት ተመ​ል​ከት” አሉ።

跟着我们:



广告