Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 3 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የሰ​ላም መል​እ​ክ​ተ​ኞች

1 እን​ዲ​ህም ብለው የሰ​ላም መል​እ​ክ​ተ​ኞ​ችን ወደ እርሱ ላኩ።

2 “እነሆ፥ እኛ የገ​ና​ናው ንጉሥ የና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ባሮች በፊ​ትህ እን​ኖ​ራ​ለን። በፊ​ት​ህም እንደ ወደ​ድህ አድ​ር​ገን።

3 እነሆ፥ ከተ​ሞ​ቻ​ች​ንና አን​ባ​ዎ​ቻ​ች​ንም ሁሉ፥ እር​ሻ​ች​ንም ሁሉ፥ መን​ጋ​ዎ​ቻ​ች​ንም፥ የመ​ሰ​ማ​ሪ​ያ​ችን ቦታ​ዎች ሁሉ፥ በጎ​ቻ​ች​ንም በፊ​ትህ ያንተ ናቸው፤ እንደ ወደ​ድ​ህም አድ​ርግ።

4 እነሆ ታላ​ላ​ቆች ከተ​ሞ​ቻ​ችን በእ​ነ​ርሱ የሚ​ኖሩ ሰዎች ባሮ​ችህ ናቸው፤ መጥ​ተ​ህም እንደ ወደ​ድህ አድ​ርግ።”

5 እነ​ዚ​ያም ሰዎች ወደ ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ደር​ሰው ይህን ነገር ነገ​ሩት።

6 እር​ሱም ወደ መን​ደ​ራ​ቸው ወረደ፤ ሠራ​ዊ​ቱም ከእ​ርሱ ጋር ወረዱ ከፍ ከፍ ያሉ አን​ባ​ዎ​ች​ንም አስ​ጠ​በቀ፥ ከእ​ነ​ር​ሱም የሚ​ረ​ዱ​ትን የተ​መ​ረጡ ሰዎ​ችን ወሰደ።

7 ወገ​ኖ​ቻ​ቸው ሁሉና እነ​ር​ሱም አክ​ሊል ደፍ​ተው እየ​ዘ​ፈኑ፥ በገና እየ​ደ​ረ​ደ​ሩና ከበሮ እየ​መቱ ተቀ​በ​ሉት።

8 እርሱ ግን አው​ራ​ጃ​ቸ​ውን ሁሉ አጠፋ፤ ጣዖ​ቶ​ቻ​ቸ​ው​ንም ሰበረ፤ አሕ​ዛ​ብም ሁሉ ናቡ​ከ​ደ​ነ​ፆ​ርን ብቻ እን​ዲ​ያ​መ​ል​ኩት፥ ቋን​ቋ​ዎ​ችና ነገ​ዶች ሁሉ አም​ላክ እን​ዲ​ሉት እርሱ የሰ​ውን ሁሉ ጣዖት ያጠፋ ዘንድ ታዝዞ ነበር።

9 በት​ልቁ በይ​ሁዳ ተራራ አን​ፃር የገ​ባ​ኢያ ዕጣ ወደ​ሚ​ሆን ወደ ኤስ​ድ​ራ​ሎ​ንም መጣ።

10 በሴ​ቅ​ቶን ከተ​ማና በጌ​ባን ሜዳ መካ​ከ​ልም ሰፈረ፤ ለሠ​ራ​ዊ​ቱም ስንቅ ያዘ​ጋጅ ዘንድ በዚያ አንድ ወር ተቀ​መጠ።

跟着我们:



广告