Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 16 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የዮ​ዲት የም​ስ​ጋና መዝ​ሙር

1 ዮዲ​ትም ይህ​ቺን የም​ስ​ጋና መዝ​ሙር በእ​ስ​ራ​ኤል ሁሉ ዘንድ ትዘ​ምር ጀመ​ረች፤ ሕዝ​ቡም ሁሉ ይህ​ቺን የም​ስ​ጋና መዝ​ሙር ከእ​ር​ስዋ ቀጥ​ለው ዘመሩ።

2 ዮዲ​ትም አለች፥ “አም​ላ​ኬን በከ​በሮ አመ​ስ​ግ​ኑት፤ ለጌ​ታ​ዬም በጸ​ና​ጽል ዘም​ሩ​ለት፤ በገና እየ​ደ​ረ​ደ​ራ​ችሁ አመ​ስ​ግ​ኑት፤ በም​ስ​ጋና ከፍ ከፍ አድ​ር​ጉት። ስሙ​ንም ጥሩ፤

3 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በጦ​ር​ነት ጦርን ያሸ​ን​ፋ​ልና።

4 ስሙም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ነው፤ ሠራ​ዊ​ቱም በሕ​ዝቡ መካ​ከል ነው፤ ከሚ​ያ​ሳ​ድ​ዱ​ኝም ሰዎች እጅ አዳ​ነኝ።

5 አሦ​ራ​ው​ያን በመ​ስዕ በኩል ከተ​ራ​ራው ወጡ፤ ከብዙ ሠራ​ዊ​ቶ​ቻ​ቸ​ውም ጋር ወጡ፤ በብ​ዛ​ታ​ቸ​ውም ፈሳ​ሹን ዘጉ። ፈረ​ሶ​ቻ​ቸ​ውም ኰረ​ብ​ታ​ውን ሸፈ​ኑት።

6 አው​ራ​ጃ​ች​ንን በእ​ሳት ያቃ​ጥሉ ዘንድ፥ ጐል​ማ​ሶ​ቻ​ች​ን​ንም በጦር ይገ​ድሉ ዘንድ፥ ሕፃ​ኖ​ቻ​ች​ን​ንም በም​ድር ላይ ይፈ​ጠ​ፍጡ ዘንድ፥ ወን​ዶች ልጆ​ቻ​ች​ን​ንና ቆነ​ጃ​ጅ​ቶ​ቻ​ች​ንን ይማ​ርኩ ዘንድ አዝ​ዘው ነበር።

7 ነገር ግን ሁሉን ቻይ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር በሴት እጅ አጠ​ፋ​ቸው።

8 አር​በ​ኛ​ቸው በጐ​ል​ማሳ እጅ ድል አል​ተ​ነ​ሣ​ምና፥ የጤ​ጣ​ኖስ ልጆ​ችም ያጠ​ፉት አይ​ደ​ሉ​ምና። ታላ​ላቁ አር​በ​ኞ​ችም ድል አል​ነ​ሡ​ትም፤ ነገር ግን የሜ​ራሪ ልጅ ዮዲት በደም ግባቷ አጠ​ፋ​ችው።

9 የመ​በ​ለ​ት​ነ​ቷ​ንም ልብስ በእ​ስ​ራ​ኤል ዘንድ ስለ​ሚ​ጨ​ነ​ቁት ሰዎች ስትል ተወች።

10 ፊት​ዋ​ንም ሽቱ ተቀ​ባች፤ ጠጕ​ር​ዋ​ንም ተሠ​ርታ ሰር​መዴ አደ​ረ​ገች፥ እር​ሱ​ንም ለማ​ሳት የተ​ልባ እግር ልብ​ስን ለበ​ሰች።

11 ጫማ​ዎ​ች​ዋም ዐይ​ኖ​ቹን በዘ​በዙ፤ ደም ግባ​ት​ዋም ሰው​ነ​ቱን ማረ​ከች፤ ሰይ​ፍም በአ​ን​ገቱ አለፈ።

12 ከመ​ደ​ፋ​ፈ​ር​ዋም የተ​ነሣ የፋ​ርስ ሰዎች ደነ​ገጡ፤ ከመ​ጨ​ከ​ን​ዋም የተ​ነሣ የሜ​ዶን ሰዎች ፈሩ።

13 ያን​ጊዜ የተ​ጨ​ነቁ ወገ​ኖች ደስ ብሏ​ቸው ደነፉ፤ የእኔ ደካ​ሞች በታ​ላቅ ድምፅ ጮኹ፤ እነ​ዚ​ያም ደን​ግ​ጠው ነበር፤ እነ​ዚ​ህም ድም​ፃ​ቸ​ውን ከፍ ከፍ አደ​ረጉ፤ እነ​ዚ​ያም ደን​ግ​ጠው ሸሹ፤

14 የሴ​ቶች ልጆች ልጆ​ችም አሳ​ድ​ደው ወጓ​ቸው፤ ጐል​ማ​ሶ​ቻ​ች​ንም አቈ​ሰ​ሏ​ቸው፤ በጌ​ታ​ዬም ጦር​ነት ጠፉ።

15 ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር መዝ​ሙር እዘ​ም​ራ​ለሁ፤ አዲስ መዝ​ሙር እዘ​ም​ራ​ለሁ፤

16 እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሆይ፥ ገናና ነህ፤ እጅ​ግም ክቡር ነህ፥ በኀ​ይ​ል​ህም የተ​ደ​ነ​ቅህ ነህ።

17 ፍጥ​ረ​ትህ ሁሉ ለአ​ንተ ይገ​ዛሉ፤ አንተ አዘ​ዝህ፤ እነ​ር​ሱም ተፈ​ጥ​ረ​ዋ​ልና፤ መን​ፈ​ስ​ህን ላክህ፤ እነ​ር​ሱም ታነጹ፥ ለቃ​ል​ህም የማ​ይ​ታ​ዘዝ የለም።

18 ተራ​ሮች ከው​ኆች ጋር ከመ​ሠ​ረ​ቶ​ቻ​ቸው ይነ​ዋ​ወ​ጣ​ሉና፤ ዐለ​ቱም ከገጸ መዓ​ትህ የተ​ነሣ እንደ አደሮ ማር ይቀ​ል​ጣ​ልና፥ ዳግ​መ​ኛም የሚ​ፈ​ሩ​ህን ይቅር በላ​ቸው።

19 መሥ​ዋ​ዕቱ ሁሉ ለበጎ መዓዛ አይ​በ​ቃ​ምና፥ ስቡም ሁሉ ከቍ​ር​ባ​ንህ ያን​ሣ​ልና። እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን የሚ​ፈ​ራው ሰው ግን ሁል​ጊዜ ገናና ነው።

20 በወ​ገ​ኖች ላይ በጠ​ላ​ት​ነት ለሚ​ነሡ ለአ​ሕ​ዛብ ወዮ​ላ​ቸው፤ ሁሉን ቻይ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም በፍ​ርድ ቀን ይበ​ቀ​ላ​ቸ​ዋል።

21 በሥ​ጋ​ቸ​ውም እሳ​ትና ትልን ይል​ክ​ባ​ቸ​ዋል፤ በመ​ከ​ራ​ውም ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ ያለ​ቅ​ሳሉ።”

22 ወደ ኢየ​ሩ​ሳ​ሌ​ምም በደ​ረሱ ጊዜ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰገዱ፤ ሕዝ​ቡም ራሳ​ቸ​ውን ባነጹ ጊዜ የሚ​ቃ​ጠ​ለ​ውን መሥ​ዋ​ዕ​ታ​ቸ​ው​ንና የፈ​ቃድ ቍር​ባ​ና​ቸ​ውን፥ ስጦ​ታ​ቸ​ው​ንም አቀ​ረቡ።

23 ዮዲ​ትም ሕዝቡ የሰ​ጧ​ትን የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒ​ስን ገን​ዘብ፥ ከመ​ኝታ ቤቱም የወ​ሰ​ደ​ች​ውን የራ​ስ​ጌ​ውን ሰይፍ ለመ​ታ​ሰ​ቢያ ለእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ሰጠች።

24 ሕዝ​ቡም በኢ​የ​ሩ​ሳ​ሌም በቤተ መቅ​ደስ ፊት ሦስት ወር ደስታ አደ​ረጉ፤ ዮዲ​ትም ከእ​ነ​ርሱ ጋር ተቀ​መ​ጠች።

25 ከእ​ነ​ዚ​ያም ወራት በኋላ ሰው ሁሉ ወደ ርስቱ ተመ​ለሰ፤ ዮዲ​ትም ወደ ቤጤ​ልዋ ተመ​ልሳ በን​ብ​ረቷ ኖረች፤ በዘ​መ​ኗም በሀ​ገሩ ሁሉ የከ​በ​ረች ሆነች።

26 የሚ​ፈ​ል​ጓ​ትም ብዙ​ዎች ነበሩ፤ ባሏ ምናሴ ሞቶ በወ​ገ​ኖቹ ዘንድ ከተ​ቀ​በረ ጀምሮ በሕ​ይ​ወት ዘመኗ ሁሉ በግ​ብር ያወ​ቃት ሰው የለም።

27 ፈጽ​ማም በክ​ብር ገነ​ነች።

28 በባሏ በም​ና​ሴም ቤት እስ​ክ​ታ​ረጅ ድረስ ኖረች፤ ዕድ​ሜ​ዋም መቶ ዐም​ስት ዐመት ነበር፤ ያች​ንም ብላ​ቴ​ና​ዋን ነጻ አወ​ጣ​ቻት፤ በቤ​ጤ​ልዋ ሞታ በባሏ በም​ናሴ ዋሻ ተቀ​በ​ረች፤

29 የእ​ስ​ራ​ኤ​ልም ወገ​ኖች ሰባት ቀን አለ​ቀ​ሱ​ላት፤ ከመ​ሞ​ት​ዋም በፊት ገን​ዘ​ብ​ዋን ለባ​ልዋ ለም​ናሴ አቅ​ራ​ቢ​ያና ለእ​ርሷ አቅ​ራ​ቢያ ለሆኑ ዘመ​ዶ​ችዋ አካ​ፈ​ለች።

30 የእ​ስ​ራ​ኤ​ል​ንም ልጆች በዮ​ዲት ዘመን፥ ዳግ​መ​ኛም እር​ስዋ ከሞ​ተች በኋላ ለብዙ ዘመን ያስ​ፈ​ራ​ቸው አል​ነ​በ​ረም።

跟着我们:



广告