Biblia Todo Logo
在线圣经

- 广告 -

本书并非出自上帝启示,且不属于基督教正典或犹太教塔纳赫的一部分。仅为历史与研究目的而展示。 查看完整说明

መጽሐፈ ዮዲት 14 - የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)


የዮ​ዲት ምክር

1 ዮዲ​ትም፥ “ወን​ድ​ሞች፥ ስሙኝ፤ ይህን ቸብ​ቸቦ ይዛ​ችሁ በግ​ንቡ ጫፍ ላይ ስቀ​ሉት።

2 ከዚህ በኋላ ሲነጋ ፀሐይ በወጣ ጊዜ ሁላ​ች​ሁም የጦር መሣ​ሪ​ያ​ች​ሁን ያዙ፤ አር​በ​ኞች የሆኑ ሰዎች ሁሉ ከከ​ተማ ወደ ውጭ ይውጡ፤ የአ​ሦ​ራ​ው​ያን ሠራ​ዊት ጠባ​ቂ​ዎ​ችም ወዳ​ሉ​በት ቦታ እን​ደ​ም​ት​ወ​ርዱ ሆና​ችሁ አለቃ ለራ​ሳ​ችሁ ሹሙ። ነገር ግን አት​ው​ረዱ።

3 ሁላ​ች​ሁም የጦር መሣ​ሪ​ያ​ች​ሁን ያዙ፥ ዘበ​ኞ​ችም ባዩ​አ​ችሁ ጊዜ የአ​ሦር ሠራ​ዊት አለ​ቆ​ችን ይቀ​ሰ​ቅሱ ዘንድ ወደ ሰፈ​ራ​ቸው ይሄ​ዳሉ፤ ከዚ​ያም በኋላ ወደ ሆሎ​ፎ​ር​ኒስ ድን​ኳን ይሮ​ጣሉ፤ አያ​ገ​ኙ​ትም፤ ከዚ​ያም በኋላ እጅግ ፈር​ተው ከፊ​ታ​ችሁ ይሸ​ሻሉ።

4 ከዚህ በኋ​ላም እና​ን​ተና በእ​ስ​ራ​ኤል አው​ራጃ የሚ​ኖሩ ሰዎች ሁሉ ተከ​ተ​ሏ​ቸው፤ በጎ​ዳ​ና​ቸ​ውም ሁሉ ርገ​ጡ​አ​ቸው።

5 ይህ​ንም ከማ​ድ​ረ​ጋ​ችሁ በፊት የእ​ስ​ራ​ኤ​ልን ወገን የካ​ደ​ውን ከእ​ኛም ጋር ይሞት ዘንድ እር​ሱን ወደ እኛ የላ​ከ​ውን እርሱ መሆ​ኑን አይቶ ያውቅ ዘንድ አሞ​ና​ዊ​ውን አክ​ዮ​ርን ጥሩ​ልኝ” አለ​ቻ​ቸው።

6 አክ​ዮ​ር​ንም ከዖ​ዝ​ያን ቤት ጠሩት፤ መጥ​ቶም የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒ​ስን ራስ በአ​ንድ ሰው እጅ ባየ ጊዜ ሰው​ነቱ ደን​ግጦ በሕ​ዝቡ ጉባኤ መካ​ከል በግ​ን​ባሩ ወደቀ።

7 በአ​ነ​ሡ​ትም ጊዜ በዮ​ዲት እግር ላይ ወደቀ፤ ሰገ​ደ​ላ​ትም፤ “ከይ​ሁዳ ቤትና ከሕ​ዝቡ ሁሉ አንቺ የተ​ባ​ረ​ክሽ ነሽ፤ ስም​ሽ​ንም ሰም​ተው ይደ​ነ​ግ​ጣሉ።

8 አሁ​ንም በእ​ነ​ዚህ ወራት ያደ​ረ​ግ​ሺ​ውን ንገ​ሪኝ” አላት። ዮዲ​ትም ከወ​ጣች ጀምሮ እስ​ክ​ት​መ​ለስ ድረስ ያደ​ረ​ገ​ች​ውን ሁሉ በሕ​ዝቡ መካ​ከል ነገ​ረ​ችው።

9 ነገ​ሯን ተና​ግራ በጨ​ረ​ሰች ጊዜ ሕዝቡ ሁሉ ቃላ​ቸ​ውን አሰ​ም​ተው ደነፉ፤ በየ​ከ​ተ​ማ​ቸ​ውም በደ​ስታ ቃል ጮኹ።

10 አክ​ዮ​ርም እግ​ዚ​አ​ብ​ሔር ለእ​ስ​ራ​ኤል ያደ​ረ​ገ​ውን ተአ​ም​ራት በአየ ጊዜ ፈጽሞ በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አምኖ ተገ​ዘረ። እስከ ዛሬም ድረስ ከቤተ እስ​ራ​ኤል ጋር አንድ ሆነ።


የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ሞት እንደ ተገ​ለጠ

11 በነ​ጋም ጊዜ የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒ​ስን ቸብ​ቸቦ በግ​ንቡ ላይ ሰቀ​ሉት፤ ወን​ዶ​ቹም ሁሉ መሣ​ሪ​ያ​ቸ​ውን ይዘው ወጡ፤ በተ​ራ​ራ​ውም ዐቀ​በት በኩል ከበ​ቧ​ቸው።

12 የአ​ሦር ሠራ​ዊ​ትም በአ​ዩ​አ​ቸው ጊዜ ወደ ሹሞ​ቻ​ቸው ላኩ፤ እነ​ር​ሱም ወደ አለ​ቆ​ቻ​ቸው፥ ወደ ሹሞ​ቻ​ቸ​ውና ገዢ​ዎ​ቻ​ቸው ሄዱ።

13 ወደ ሆሎ​ፎ​ር​ኒ​ስም ድን​ኳን መጥ​ተው ለመ​ጋ​ቢው፥ “እነ​ዚህ ባሮች እስከ መጨ​ረ​ሻው ይጠፉ ዘንድ ሊዋ​ጉን ተደ​ፋ​ፍ​ረው ወር​ደ​ዋ​ልና ጌታ​ች​ንን ከእ​ን​ቅ​ልፉ ቀስ​ቅ​ሰው” አሉት።

14 ባግ​ዋም ከዮ​ዲት ጋር የተኛ መስ​ሎ​ታ​ልና ገብቶ በድ​ን​ኳኑ አን​ጻር ያለ በሩን መታ።

15 ቃል የሚ​መ​ል​ስ​ለት ሰውም በአጣ ጊዜ ድን​ኳ​ኑን ተር​ትሮ ወደ እል​ፍኙ ገባ፤ ሬሳ​ው​ንም በወ​ለሉ ላይ ወድቆ አገ​ኘው። ራሱም በላዩ አል​ነ​በ​ረም።

16 እያ​ለ​ቀ​ሰና እያ​ቃ​ሰተ በታ​ላቅ ቃል ፈጽሞ ጮኸ፤ ልብ​ሱ​ንም ቀደደ።

17 ዮዲ​ትም ወደ​ም​ታ​ድ​ር​በት ድን​ኳን ገባ፤ ነገር ግን አላ​ገ​ኛ​ትም፤ ወደ ሕዝ​ቡም እየ​ሮጠ ሄዶ ጮኸ​ላ​ቸው። እን​ዲ​ህም አላ​ቸው፦

18 “እነ​ዚህ ባሮች አታ​ለ​ሉን፤ እነሆ፥ የሆ​ሎ​ፎ​ር​ኒስ ሬሳው በም​ድር ላይ ወድ​ቋ​ልና፥ ራሱም በላዩ የለ​ምና አን​ዲት ዕብ​ራ​ዊት ሴት በን​ጉሡ በና​ቡ​ከ​ደ​ነ​ፆር ቤት ላይ ኀፍ​ረ​ትን አድ​ር​ጋ​ለች።”

19 የአ​ሦር የሠ​ራ​ዊት አለ​ቆ​ችም ይህን ነገር በሰሙ ጊዜ ልብ​ሳ​ቸ​ውን ቀደዱ፤ ሰው​ነ​ታ​ቸ​ውም ፈጽማ ደነ​ገ​ጠች፤ በታ​ላቅ ድም​ፅም በሰ​ፈር መካ​ከል ፈጽ​መው ጮኹ።

跟着我们:



广告